ብልጽግና ፓርቲ ለተለያዩ የስራ ሃላፊዎች ሹመት ሰጠ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ብልጽግና ፓርቲ ለተለያዩ የስራ ኃላፊዎች ሹመት መስጠቱን ፓርቲው በዛሬው እለት አስታውቋል።
በዚህም መሰረት፡–
- አቶ መለስ አለሙ- የአዲስ አበባ ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ
- አቶ ተስፋዬ በልጅጌ- በብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት የፖለቲካና ርዕዮተ አለም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ
- ዶክተር ቢቂላ ሁሪሳ- በብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት የአለም አቀፍና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ሃላፊ ሆኖ ተመድበዋል።
#FBC
የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።