Fana: At a Speed of Life!

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የስቅለት በዓል ተከበረ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እምነት ተከታዮች ዘንድ የኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት በዓል ተከብሯል።

በዕለቱ ቀኑን የሚያወሱ የመፅሀፍ ቅዱስ ክፍሎች የተነበቡ ሲሆን፥ ዕለቱ ስቅለት ፍቅር፣ ይቅር ባይነትና ትሕትና በተግባር የተገለጠበት መሆኑ ተገልጿል።

የቤተክርስቲያኗ አባቶች የኢየሱስ ክርስቶስ ስቅለት አስተምህሮ ፍቅር፣ ይቅር ባይነትና ትሕትናን በተግባር የተገለጠበት ዕለት እንደሆነም ትምህርተ ወንጌል ሰጥተዋል።

ቤተክርስቲያኗ ዕለቱን በስግደት፣ በጾምና ፀሎት ሥነ ሥርዓት የምታስበው ክርስቶስ ለሰው ልጆች ነፃ መውጣት የከፈለውን ዋጋ በማሰብ እንደሆነ ተመላክቷል።

የቤተክርስቲያኗ አባቶች የክርስቶስ መስቀል ፍቅር፣ አንድነትና ይቅር ባይነት የተገለጠበት መሆኑን በማንሳት÷ ከክርስቶስ ፍቅርን እና ፍጹም ይቅር ባይነትን የምንማርበት የመዳን ቀን ነው ብለዋል።

የመፋቀር፣ መተሳሰብ እና የአብሮነትን ተምሳሌት ማድረግ እንደሚገባም ነው ያስገነዘቡት፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.