Fana: At a Speed of Life!

በሽንሌ ከተማ በ100 ሚሊየን ብር የተገነባው ኦክስጅን ፋብሪካ ተመረቀ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሶማሌ ክለል ሽንሌ ከተማ በፋራሕ ዋይስ ዱሌ አጠቃላይ ሆስፒታል የተገነባው የኦክስጅን ማምረቻ ፋብሪካ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ተደርጓል፡፡
በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ በም/ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልጽግና ፓርቲ ም/ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ እና የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሃመድ ተገኝተዋል፡፡
የኦክስጅን ፋብሪካው ለሲቲ ዞን ሁሉም ጤና ተቋማትና ለምስራቅ ኢትዮጵያ አካባቢዎች ኦክስጅን ማዳረስ እንደሚያስችል የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ አመላክቷል፡፡
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.