Fana: At a Speed of Life!

በሺያመን ዳይመንድ ሊግ አትሌት አዲሱ ይሁኔ አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ2026 የዳይመንድ ሊግ ሁለተኛ መዳረሻ በሆነችው የቻይናዋ ሺያመን ከተማ በወንዶች 5 ሺህ ሜትር አዲሱ ይሁኔ አሸንፏል።

አትሌት አዲሱ 12፡57.32 በሆነ ሰዓት ውድድሩን ያጠናቀቀ ሲሆን ይህም የዓመቱ የዓለማችን ፈጣኑ ሰዓት እንዲሁም የውድድሩ አዲስ ክብረ ወሰን ሆኖ ተመዝግቧል።

ሌላኛው ኢትዮጵያዊው አትሌት ቢኒያም መሐሪ 3ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቅቋል፡፡ በሴቶች 1 ሺህ 500 ሜትር በለፈው ሳምንት በሻንግሀይ ዳይመንድ ሊግ ያሸነፈችው አትሌት ብርቄ ሀየሎም በዛሬው ዕለት 2ኛ ደረጃን ይዛ ጨርሳለች።

አትሌት ሳሮን በርሄ 6ኛ እና አትሌት ወርቅነሽ መሰለ 15ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቅቀዋል፡፡

በሴቶች 3 ሺህ ሜትር መሰናክል ውድድር የተሳተፉት አትሌት ኬና ቱፋ 5ኛ፣ አትሌት ዓለምናት ዋለ 8ኛ እና አትሌት ፍሬሕይወት ገሰሰ 9ኛ ሆነው ውድድሩን ጨርሰዋል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.