አልቫሮ አርቤሎአ የፉልሃም አሰልጣኝ ሆኖ ተሾመ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የእንግሊዙ ክለብ ፉልሃም አልቫሮ አርቤሎአን የክለቡ ዋና አሰልጣኝ አድርጎ መሾሙን ይፋ አድርጓል፡፡
በዚህ መሰረትም አልቫሮ አርቤሎአ አሰልጣኝ ማርኮ ሲልቫን በመተካት በክራቨን ኮቴጅ የሚያቆየውን የ3 ዓመት ኮንትራት ተፈራርሟል፡፡
የ43 ዓመቱ አልቫሮ አርቤሎአ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በሊቨርፑል እና ዌስትሃም ክለቦች መጫዎቱ ይታወሳል፡፡
በመልካም ፈቃዱ