Fana: At a Speed of Life!

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር) የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ሂደትን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች:-

👉 ቡድኖች በሂደቱ ከተነጋገሩ በኋላ እያንዳንዱ የሄዱበትን ሂደት በቃለጉባኤ ይያዝና ተፈራርመው ወደሚቀጥለው ያልፋል፡፡
👉 ወደ ስልታዊ ቡድን ሲመጡ 50 ሆነው አምስቶቹ የተወያዩበትን ለ250 የሚያቀርቡበት፤ በዛ ላይ የሚወያዩበት፤ ይሄ ቀረ የሚሏቸውን ሀሳቦች የሚያካትቱበት ነው፡፡
👉 10 በነበሩበት ጊዜ ያቀረቧቸው ሀሳቦች ትዝ ሲሏቸው 50 ላይ በነበሩበት ጊዜ ያቀረቧቸው ሀሳቦች በሚገባ አለመካተታቸውን ሲያስተውሉ እንደገና እንዲዳብሩ የሚያደርጉበት ነው፡፡
👉 ሁሉም 250ዎች ማለትም 16ቱም በያሉበት ቡድን ይፈራረማሉ፡፡
👉 ሀሳቤ ይሄ ነው፤ ወደመሃል ያመጡን ሃሳቦች ደግሞ እነኚህ ናቸው ብለው የሚግባቡባቸውን በሙሉ በየቡድኑ በተመደቡ አጠናቃሪዎች አሉ ካጠናቀቁ በኋላ ወደ 500ዎቹ ይሄዳሉ፡፡
👉 አንዳንዶቹ ነገሮች በቶሎ የሄዱላቸው ቡድኖች አሉ እንደገና ሀሳባቸውን እያመጡ እያስተካከሉ እያዳበሩ ዛሬ ሁሉም 16ቶቹም ተፈራርመው ይጨርሳሉ ብለን እንጠብቃለን፡፡
👉 ተፈራርመው ከጨረሱ በኋላ አንድ አጀንዳ ላይ ወደሚወያዩበት ትልቁ የ500 ጉባኤ ይሄዳሉ፡፡
👉 የ500 ጉባኤ ሙሉ በሙሉ የሚሳካ ከሆነ ነገ ይጀምራል፤ ዛሬ የሚያድር አጀንዳ ያላቸውም ካሉ ወደሚቀጥለው ቀን ይዘዋወራል፡፡
👉 4 ሺዎቹ አንድ ላይ አዳራሽ ይገናኙና ስለ 500ው ሂደት ገለጻ ይደረግላቸዋል፡፡
👉 500ዎቹ ከተጀመረ በኋላ ሙሉውን ሂደት በደንብ የምናሳውቅ ይሆናል፡፡
👉 ባለሙያዎች ለሁሉም መሰረታዊ እውቀት አስጨብጠዋል ብዬ አምናለሁ፤ አንዳንድ ጊዜ የዘመሙ ሁኔታዎች ሲስተዋሉ የእርምት እርምጃ እንዲወሰድ እናደርጋለን፡፡
👉 እዚህ የመጡት ለሀገር ጉዳይ ነው ለብዙ ዘመን ተቋጥረው የነበሩ ብሶቶቻቸውን፤ ችግሮቻቸውን ይዘው መጥተው በዚህ መድረክ ላይ እንዲታወቁላቸው ለማድረግ ብዙ ትግል ቢያደርጉም ትልቁ ስዕል ኢትዮጵያ መሆኗን በሚገባ ይገነዘባሉ፡፡
👉 የተሰጣቸውን ሁሉ ይጋታሉ ብላችሁ አትጠብቁ፤ ብዙ እውቀት ከገጠር እስከ ከተማ ኢትዮጵያ ውስጥ አለ የሚጠመዘዙ አይደሉም፡፡
👉 ሊያሳኩ የሚፈልጉት ነገር ኢትዮጵያ በተባለችው ሀገር ዙሪያ ነው፡፡
👉 ቃለ ጉባኤ ያዦች በትልልቅ ተቋማት የሰሩ ትልቅ ልምድ ያላቸው አንቱ የተባሉ ሰዎች ናቸው፡፡
👉 ስህተቶችን ከስር ከስር እየተከታተልን የምናርም ነው የሚሆነው፤ ምክክር ሂደት ነው፤ ይሄ ምክክር ለሀገራችን የመጀመሪያ ነው፡፡
👉 ምንም ቢሆን አንዳችን ሌሎቻችን ላይ ጫና መፍጠር የለብንም፤ ምክክር ማለት መከባበር፣ መነጋገር፣ መደማመጥና ወደ መካከል መምጣት ማለት ነው።
በመልካም ፈቃዱ
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.