ሚኒስቴሩ በአዲስ አበባ ለሚገኙ ኤምባሲዎች ለአዲሱ ዓመት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት እያስተላለፈ ነው
አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ላደረጉ የተለያዩ ሀገራት ኤምባሲዎች ለመጪው የኢትዮጵያ አዲስ ዓመት በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት እያስተላለፈ ይገኛል፡፡
በዚህም መሰረት የሚኒስቴሩ ተወካዮች በአካል በመገኘት ለዮርዳኖስ እና ኢኳቶሪያል ጊኒ ኤምባሲዎች ለአዲሱ ዓመት መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡
በፍቅርተ ከበደ