Fana: At a Speed of Life!

የኢፌዴሪ አየር ኃይል የጽናት ቀንን አከበረ

አዲስ አበባ፣ጳጉሜን 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጳጉሜን 3 – የጽናት ቀን በኢፌዴሪ አየር ኃይል ጠቅላይ መምሪያ በተለያዩ መርሐ ግብሮች ተከብሯል፡፡

አየር ኃይሉ የጀግኖችን ፅናት ተላብሶ የተሰጠውን ተልዕኮ በብቃት፤ በቁርጠኝነትና በታማኝነት እየተወጣ እንደሚገኝ በመርሐ ግብሩ ላይ ተመላክቷል፡፡

ሠራዊቱ በዲሲፕሊንና በሙያዊ ብቃት እንዲሁም በአንድነት ለተሰጠው አደራና ለዘላቂ ተቋም ግንባታ ጉዞውን አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም ነው የተገለጸው፡፡

የፅናት ቀን የትናንቱን የጀግንነት ታሪክ በማስታወስ አርበኞችና ጀግኖች የሚዘከሩበት እንዲሁም ዛሬ ያለውን የሠራዊቱን ፅናት በማስቀጠል ለሀገር የተገባው ቃል የሚታደስበት የዕምነትና የአደራ ቀን መሆኑም ተገልጿል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.