Fana: At a Speed of Life!

በኦሮሚያ 1 ነጥብ 8 ሚሊየን ለሚሆኑ ተማሪዎች ድጋፍ ለማድረግ ገቢ እየተሰበሰበ መሆኑ ተገለፀ

አዲስ አበባ ፣ መስከረም 18 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ)በ ኦሮሚያ 1 ነጥብ 8 ሚሊየን ለሚሆኑ ተማሪዎች ድጋፍ ለማድረግ ገቢ እየተሰበሰበ መሆኑ ተገለፀ።
“እኔ ለአንድ ተማሪ” በሚል መሪ ሃሳብ የኦሮሚያ ክልል ሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ቢሮ÷ የትምህርት ቁሳቁስ መግዛት ለማይችሉ 1 ነጥብ 8 ሚሊየን ለሚሆኑ ተማሪዎች ድጋፍ ለማድረግ የገቢ ማሰባሰብ ሥራውን እያከናወነ መሆኑን ገልጿል።
በዛሬው ዕለት የተጀመረው የገቢ ማሰባሰብ ሥራው ለአንድ ሳምንት የሚቆይ ነው ተብሏል።
ከኦሮሚያ የተለያዩ ቢሮዎች በአንድ ቀን ብቻ 4 ነጥብ 1 ሚሊየን ብር መሰብሰብ መቻሉም ነው የተገለጸው ።
የገቢ ማሰባሰብ ሂደቱ በክልል፣ በዞን፣ በወረዳ እና በቀበሌ እንደሚከናወን እና ዓመቱን በሙሉ ለተማሪዎች የቁሳቁስ ድጋፉ እንደሚደረግም ተነግሯል።
ከትምህርት ቁሳቁስ ባለፈም የኮቪድ-19 መከላከያ ድጋፍ እንደሚደረግላቸው መገለጹን ከትምህርት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.