Fana: At a Speed of Life!

የተመድ የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን በኢትዮጵያ አሁናዊ ሁኔታ ላይ የሚለቀቁ ሀሰተኛ መረጃዎች ላይ ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ አሳሰበ

አዲስ አበባ ፣ህዳር 3 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ )የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽን በኢትዮጵያ አሁናዊ ሁኔታ ላይ የሚለቀቁ ሀሰተኛ መረጃዎች ላይ ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ አሳሰበ ።
ድርጅቱ አያይዞም ሱዳን በሚገኘው የኮሚሽኑ ህጋዊ የቲዊተር ገጽ እንደተለጠፈ ተደርጎ የቀረበው ምስል ሀሰተኛ ነውም ሲል አስታውቋል።
በዚህም በኢትዮጵያ እና በሱዳን አሁናዊ ሁኔታ ላይ የሚለቀቁ ሀሰተኛ መረጃዎች ላይ ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ አስጠንቅቋል።
በመሆኑም ድርጅቱ በማኅበራዊ የትስስር ድረ ገጾች ላይ መረጃዎችና ምስሎችን ከማውጣትና ከማጋራት በፊት ማረጋገጥ፣ ሀላፊነት መውሰድና ጥንቃቄ ማድረግ ይገባልም ነው ያለው።
የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.