ጊዜያቸው ያላለፈባቸውን የሬዲዮ መገናኛዎች ኮሚቴ አቋቁመው ለህወሃት የፀረ-ሰላም ቡድን የላኩ መኮንኖች ፍርድ ቤት ቀረቡ
በተለይም ምርመራው በጅምላ ነው እየተከናወነ ያለው በተናጠል ተሳተፏቸው አልተገለጸም ከማን ጋር ማን የሚለው ተሳተፎ ባልተገጸበት ሁኔታ ተጨማሪ ጊዜ መጠየቁ አግባብነት የለውም ብለዋል።
ተጠርጣሪዎቹ የመገናኛ ሬዲዮ ኔትወርክ የማቋረጥ ስልጣን የላቸውም ከወንጀሉ ጋር ግንኙነት የላቸውም በመታሰራቸው ቤተሰቦቻቸው ተቸግረዋል ፍርድቤቱ ይህን ተረድቶ በዋስ ወጥተው በቤታቸው ሆነው ምርመራው ይቀጥል ከሃገር እንዳይወጡ እግድ ሊጣል ይቻላል ሲሉም ጠበቆቻቸው የዋስትና ጥያቄ አንስተዋል።
መርማሪ ፖሊስም ከሃገር እንዳይወጡ ታገደውም በዋስ ቢወጡ በመከላከያ ስራ ላይ ያሉ በተለያየ አጋጣሚ የሚያወቋቸው ስላሉ ምስክርም ሆነ ማስረጃ ሊያሸሹ ይችላሉ ሲል ተቃውሟል።
1ኛ ተጠርጣሪ ሜጀር ጄኔራለ ገብረመድህን የአዲስ አባባ ዩኒቨርስቲ የማስተርስ ፕሮግራም ትምህርታቸውን ለመከታተለ ፎርም እንዲሞሉ ይፈቀድ ሲሉ ያመለከቱ ሲሆን÷ 5ኛ ተጠርጣሪ ብርጋዴል ጄኔራለ ፈስሃ ገ/ስላሴ የልብና የደም መርጋት ህመምተኛ መሆናቸወን ጠቅሰው የፌዴራል ፖሊስ ወስዶ በፖሊስ ሆስፒታል እንዳሳከማቸው ገልጸው ነገር ግን አጠቃላይ አልትራ ሳወንድ ምርመራ ለማድረግ ወደ ህዳሴ እንዲላኩ ጠይቀዋል ፍርድቤቱም የሪፈር ትዛዝ በሌለበት ሁኔታ እንዴት እኔ ሪፈር ብዬ ፈቅዳለው ሲል ምላሽ ሰጥቷል።
የተጠርጣሪዎቹ የልጆቻቸው የትምህርት ቤት መጠቀሚያ የሚውለው ላፕቶፖቻቸው ለምርመራ ተውስዷል ቢመለስ የሚል ጥያቄም አንስተዋል።
ችሎቱም መዝገቡን መርምሮ ትዛዝ ለመስጠት ለታሳስ 15 ተለዋጭ ቀጠሮ ሰቷል።