Fana: At a Speed of Life!

የውሃ አካል ዳርቻ ክልልን ለመወሰን በወጣው ረቂቅ አዋጅ ላይ የባለሙያዎች ውይይት እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥር 24፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የውሃ አካል ዳርቻ ክልልን ለመወሰን በወጣው ረቂቅ አዋጅ ላይ የባለሙያዎች ውይይት በባሕር ዳር እየተካሄደ ነው።

በውይይቱ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተፈጥሮ ሃብት፣ መስኖና ኢነርጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወይዘሮ ፈቲያ የሱፍን ጨምሮ ጉዳዩ የሚመለከታቸው የፌደራልና የክልል ባለድርሻ አካላትና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተሳታፊዎች ናቸው።

በረቂቅ አዋጅ ላይ የሚደረገው የባለ ድርሻ አካላት እና ምሁራን ውይይት ተጨማሪ ግብዓት ለማግኘት እና በሚሻሻሉ ጉዳዮች ዙሪያ መረጃ ለመሰብሰብ ያለመ መሆኑን የተፋሰሶች ልማት ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ግዛው ተናግረዋል።

ረቂቅ አዋጁ በስድስት ክፍሎች እና በ28 አንቀጾች ተከፍሎ የቀረበ ሲሆን 23 ሙያዊ ቃላትም ትርጓሜ እንደተዘጋጀላቸው ተገልጿል።

በናትናኤል ጥጋቡ

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤
ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ
ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.