ሀገራችንን ለአሸባሪው ቡድን አሳልፈን አንሰጥም – የመተከል ዞን ወጣቶች
አዲስ አበባ፣ መስከረም 12፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ) “ ሀገራችንን ለአሸባሪው ቡድን አሳልፈን አንሰጥም ” ያሉ የመተከል ዞን ወጣቶች ወደ ውትድርና ማስልጠኛ አሸኛኘት ተደርጎላቸዋል።
በሽኝት ፕሮግራሙ ላይ የቤኒንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሰላም ግንባታና ፀጥታ ቢሮ ሃላፊ አቶ አብዮት አላብሮ ፥ ምንጊዜም ከኢትዮጵያ አብራክ የተገኙ ጀግኖች ሀገራችንን አሳፍረዋት አያውቁም ብለዋል።
የመተከል ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጋሹ ዱጋዝ በበኩላቸው ፥ በአሸባሪው የህወሓት ቡድን የተደቀነውን ኢትዮጵያን የማፍረ አደጋ የዞናችን ወጣቶች ከጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ጎን ተሰልፋችሁ ለመደምስ ወደ ስልጠና ስሸኛችሁ በደስታ ነው ብለዋል።
በስፍራው የሚገኘው ክፍለ ጦር አመራር በበኩላቸው ፥ እናንተ የአባቶቻቹሁን አደራ ጠባቂ ልጆች ሀገርን ያለ ማስደፈር የደም ውርስ ከጀግኖች አባቶቻችሁ ወርሳችሁ፥ አሸባሪውን ለመመከት መዘጋጀታችሁ ያኮራል ማለታቸውን ከመከላከያ ሠራዊት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!