ብሔራዊ ባንክ የብድር ገደብ ላይ ማሻሻያ አደረገ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 25፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በቅርቡ ከብድር አቅርቦት ጋር በተያያዘ የጣለውን እገዳ ማሻሻያ ማድረጉን አስታውቋል፡፡
በማሻሻያው ባንኮች አምስት የብድር ዓይነቶችን መፍቀድ እንደሚችል አሳዉቋል፡፡
እነዚህም ባንኮች የሰጡትን ብድር ለማስመለስ ሐራጅ ያወጧቸውን ንብረቶች ለመግዛት ለሚጠይቁ ገዥዎች ስለሚሰጥ ብድር ፣ በሁለተኛና በሦስተኛ ወገን መካከል የሚደረግ ግብይትና ለባንክ ሠራተኞች ስለሚሰጥ አስቸኳይ ብድር ነው፡፡
እነዲሁም ቅድመ ሁኔታዎችን አሟልተው መኖርያ ቤት ለመግዛት ወይም ለመገንባት ከታመነባቸው ጠያቂዎች ስለሚሰጥ ብድር፣ ከፀደቁ ድርጅቶችና ከተቋም ሠራተኞች ለሚቀርቡ የብድር ጥያቄዎች እንዲሁም በጎንደር አካባቢ ለሚገኙ የሰሊጥ አምራች ብድር ጠያቂዎች ላይ ማሻሻያዎች መደረጉን ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ያገኘነዉ መረጃ ያመላክታል።
በዚህም በእነዚህ የብድር ዓይነቶች ላይ ብድር መስጠት እንደሚችል ተገልጿል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!