Fana: At a Speed of Life!

በኦሮሚያ ክልል በ20 ከተሞች ሕዝባዊ ውይይት ይካሄዳል

አዲስ አበባ፣ የካቲት 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል በሁሉም ዞኖች በሚገኙ 20 ከተሞች በነገው ዕለት ሕዝባዊ ውይይት ይካሄዳል፡፡ በውይይት መድረኩ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ከሕብረተሰቡ ጋር ይመክራሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ለውይይት መድረኩም የተለያዩ…

ፕሬዚዳንት ዘሌንስኪ የዩክሬን ጦር ዋና አዛዥን ከሥራ አሰናበቱ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 01፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የዩክሬን ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዘሌንስኪ የሀገሪቱን ጦር ዋና አዛዥ ጄነራል ቫለሪ ዛሉዥኒን ከሥራ ማሰናበታቸው ተሰምቷል፡፡ ፕሬዚዳንት ዘሌንስኪ ዋና አዛዡን ከሥራ ያሳናበቱት በመካከላቸው የሃሳብ ልዩነት መፈጠሩን ተከትሎ ነው ተብሏል፡፡…

ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) የትግራይ ክልል የመልሶ ግንባታና የሰላም ስምምነት አፈጻጸምን እየገመገሙ ነው

አዲስ አበባ፣ የካቲት 01፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ የነበሩትን ሥራዎች እና መሻሻሎች በጥልቀት መገምገም ጀምረዋል። ይህ በፌደራል እና የክልል ኃላፊነት ባላቸው የሥራ ተዋንያን የሚደረገው ጠቃሚ…

የኢትዮጵያና ፓኪስታን ወታደራዊ ዩኒቨርሲቲዎች በጋራ መሥራት በሚችሉበት ሁኔታ ላይ ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 01፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ የፓኪስታን አምባሳደር አቲፍ ሻሪፍ የተመራ ልዑክ ከኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ኮማንዳንት ብርጋዲየር ጄኔራል ከበደ ረጋሳ ጋር ተወያይተዋል፡፡ ውይይቱ በሁለቱ ሀገራት የተቋማት ግንኙነትና የጋራ ጥቅም ትብብር ላይ ያተኮረ መሆኑን…

ጠቅላይ ፍ/ቤት በእነ ዶ/ር ወንድወሰን መዝገብ በሽብር ወንጀል የተከሰሱ 27 ግለሰቦች ክሳቸው እንዲቋረጥ በስር ፍ/ቤት የተሰጠውን ብይን ሻረ

አዲስ አበባ፣ ጥር 30፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ፍርድ ቤት በእነ ዶ/ር ወንድወሰን አሰፋ መዝገብ በሽብር ወንጀል የተከሰሱ 27 ግለሰቦች ክሳቸው እንዲቋረጥ በስር ፍርድ ቤት የተሰጠውን ብይን ሻረ። ጠቅላይ ፍ/ቤቱ ከ6 ወራት በፊት በአማራ ክልል ተከስቷል ከተባለው ሁከትና አመጽ ጋር ተያይዞ…

በአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ አንቶኒዮ ጉተሬዝን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራትና ተቋማት መሪዎች ይሳተፋሉ

አዲስ አበባ፣ ጥር 30፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራትና ተቋማት መሪዎች እንደሚሳተፉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ አለም (ዶ/ር)…

ሹመቱ የብልጽግና ፓርቲ አመራሮች ሲመክሩበት ቆይተው የወሰኑት መሆኑን ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) ገለጹ

አዲስ አበባ፣ ጥር 30፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በዛሬው ዕለት የተሰጠው ሹመት የብልጽግና ፓርቲ አመራሮች ሲመክሩበት ቆይተው የወሰኑት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን ያሉት 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን በ15ኛ መደበኛ…

አቶ ተመስገን ጥሩነህ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ተሾሙ

አዲስ አበባ፣ ጥር 30፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የስራ ዘመን በ15ኛ መደበኛ ስብሰባው የአቶ ተመስገን ጥሩነህን ሹመት አጽድቋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአቶ ተመስገንን የሥራ ልምድ ዘርዝረው ለምክር ቤቱ ባቀረቡት መሰረት ምክር ቤቱ…

የመዲናዋ ሆቴሎች የአፍሪካ መሪዎች ጉባኤ እንግዶችን ለማስተናገድ ዝግጅት አጠናቅቀዋል

አዲስ አበባ፣ ጥር 30፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በመዲናዋ የሚገኙ ሆቴሎች ለአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የሚመጡ እንግዶችን ለማስተናገድ አስፈላጊውን ዝግጅት ማጠናቀቃቸውን የአዲስ አበባ ሆቴል ባለቤቶች ማህበር አስታውቋል፡፡ የማህበሩ ፕሬዚዳንት ወ/ሮ አስቴር ሰለሞን እንዳሉት÷ የመዲናዋ ሆቴሎች…

አየር ሃይል ዘመኑ የደረሰበትን ትጥቅ እስከመታጠቅ የደረሰ የሀገር ኩራት ተቋም ሆኗል – ሌ/ጀ ይልማ መርዳሳ

አዲስ አበባ፣ ጥር 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) አየር ሃይል ዘመኑ የደረሰበትን ትጥቅ እስከመታጠቅ የደረሰ የሀገር ኩራት ተቋም ነው ሲሉ የኢፌዴሪ አየር ሃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጀኔራል ይልማ መርዳሳ ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ70ኛ ቃኘው ኮርስ ዕጩ መኮንኖችና አሰልጣኞች በአየር…