Fana: At a Speed of Life!

ገቢ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት እራስን ለመቻል በቁርጠኝነት መስራት ይገባል – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት እራስን ለመቻል በዘርፉ የተጀመረውን ሥራ ይበልጥ ማጠናከር ይገባል አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በሁዋጂያን ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ውስጥ የሚገኘውን…

የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ከ117 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ አገኘ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ117 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ አገኘ፡፡ የድርጅቱ የበጀት ዓመት የሶስተኛ ሩብ ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ተካሂዷል፡፡ በዚህ ወቅት የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና…

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ጎበዝ ሶላር ሴል ማምረቻን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአዲስ አበባ በሁዋጂያን ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ውስጥ የሚገኘውን "ጎበዝ ሶላር ሴል" ማምረቻን ጎብኝተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት እንዳሉት÷ ይህ ፋብሪካ በ2025…

ምርጫ ለአንድ ሀገር ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ መሠረት ነው – ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ምርጫ የሕዝብ ሉዓላዊነት የሚገለጽበትና ሕዝብ በድምፁ መንግሥት የሚመሠርትበትም ሒደት ነው አሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፡፡ የብልጽግና ፓርቲ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የምረጡኝ ቅስቀሳ መርሐ ግብር በአዲስ አበባ ስታዲየም ተካሂዷል፡፡ ከንቲባ…

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 54 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ያልተጣራ ትርፍ አገኘ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተያዘው በጀት ዓመት ባለፉት 9 ወራት 54 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ያልተጣራ ትርፍ አስመዘገበ፡፡ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሶስተኛ ሩብ ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ተካሂዷል፡፡ የባንኩ ፕሬዚዳንት አቤ ሳኖ…

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመጋቢት እና ሚያዝያ 2018 ዓ.ም ወራት ያከናወኗቸው ተግባራት

በመጋቢት እና ሚያዝያ 2018 ዓ.ም ወራት፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሳይንሳዊ የምርምር ልህቀት፣ በከተማ ልማት፣ በኢኮኖሚ ሪፎርም እና በቀጣናዊ ዲፕሎማሲ ዙሪያ ያተኮሩ የተለያዩ ከፍተኛ የሥራ ክንውኖችን አድርገዋል። ‎ ‎• የፕሮጀክቶች ምረቃ እና የሥራ ጅማሮ ‎የመጋቢት ወር…

በመዲናዋ በሁሉም ዘርፎች የተገኙ ውጤቶችን ለማስቀጠል በትኩረት ይሰራል – ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሁሉም ዘርፎች የተገኙ ውጤቶችን ለማስቀጠል በትኩረት ይሰራል አሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፡፡ የብልጽግና ፓርቲ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የምረጡኝ ቅስቀሳ መርሐ ግብር በአዲስ አበባ ስታዲየም ተካሂዷል፡፡ ከንቲባ…

ነገሌ አርሲና ፋሲል ከነማ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ29ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ነገሌ አርሲ እና ፋሲል ከነማ ያለምንም ግብ አቻ ተለያይተዋል፡፡ ቀን 9 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ሁለቱም ቡድኖች ግብ ሳያስቆጥሩ…

የጋምቤላ ክልል 5 ሺህ 535 ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ አስገባ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ከጋምቤላ ክልል ባለፉት 9 ወራት 5 ሺህ 535 ኪሎ ግራም የወርቅ ምርት ለብሔራዊ ባንክ ገቢ ተደርጓል አለ የክልሉ ማዕድን ቢሮ፡፡ የቢሮው የ2018 በጀት ዓመት 9 ወራት እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አለሚቱ ኡሞድ በተገኙበት…

በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በመራጮች ትምህርት ላይ የሚሠማሩ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ይፋ ሆኑ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በመራጮች ትምህርት ላይ ለሚሠማሩ 169 የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ዕውቅና መስጠቱ ይታወቃል። ቦርዱ በዛሬው ዕለትም በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በመራጮች ትምህርት ላይ የሚሠማሩ የሲቪል ማኅበረሰብ…