Fana: At a Speed of Life!

ዳያስፖራዎች የቦሌ ለሚና ቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርኮችን እየጎበኙ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥር 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ዳያስፖራዎች የቦሌ ለሚና የቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርኮችን እንዲሁም የአይ ሲ ቲ ፓርክን እየጎበኙ ነው፡፡ የጉብኝት መርሃ ግብሩ ዳያስፖራዎች በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ የኢንቨስትመንት አማራጮችን እንዲመለከቱ ያለመ መሆኑ ተገልጿል፡፡ የኢንዱስትሪ…

ቻይና የክረምቱን የቤጂንግ ኦሎምፒክ ጨዋታ ለመዘገብ የሚመጡ ሚዲያዎችን በደስታ እንደምትቀበል ገለጸች

አዲስ አበባ፣ ጥር 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ቻይና የቤጂንግ የክረምት ኦሎምፒክ ጨዋታዎችን ሊዘግቡ ከተለያዩ ሀገራት የሚመጡ ሚዲያዎችን በደስታ እንደምትቀበል የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ ዋንግ ዌንቢን ገለጹ፡፡ ገንቢ ሀሳቦችን የሚያቀርቡ ጋዜጠኞችን ቻይና የምታበረታታ ሲሆን፥…

አቶ ደመቀ መኮንን ከኖርዌይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር በስልክ ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ጥር 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ከኖርዌይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አኒከን ሁይትፌልድት ጋር በስልክ ተወያዩ። አቶ ደመቀ ለኖርዌይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በኢትዮጵያ እየታዩ ስላሉ ለውጦች ገለጻ አድርገዋል።…

”የዳያስፖራው ሚና በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ዘርፍ” በሚል ርእስ ውይይት እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥር 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ''የዳያስፖራው ሚና በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ዘርፍ'' በሚል ርእስ በአዲስ አበባ ውይይት እየተካሄደ ነው። በመድረኩ ኢትዮጵያ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ እንድትሆን በኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዘርፍም የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑ…

አሸባሪው ህወሃት ለትግራይ ህዝብ ሰብዓዊ ድጋፍ እንዳይቀርብ እንቅፋት መሆኑን እንደቀጠለበት መንግስት ገለፀ

አዲስ አበባ፣ ጥር 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) አሸባሪው የህወሃት ቡድን ለትግራይ ህዝብ ሰብዓዊ ድጋፍ እንዳይቀርብ እንቅፋት መሆኑን መንግስት ገለፀ። የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ባወጣው መግለጫ፥ የአሸባሪው የህወሃት ቡድን የትግራይን ህዝብ በስም ለመነገጃነት ከማዋል ውጪ ቆሜለታለሁ ብሎ…

በደብረ ብርሃን በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ነዋሪዎችን የሚያሳትፍ የሴፍቲኔት ፕሮጀክት ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ ጥር 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በደብረ ብርሃን ከተማ በ10 ነጥብ 8 ሚሊየን ብር በጀት በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ከ1 ሺህ 600 የሚልቁ ነዋሪዎችን የምግብ ዋስትና በማረጋገጥና በስራ እድል ፈጠራ ተጠቃሚ የሚያደርግ የሴፍቲኔት ፕሮጀክት ተጀመረ። የደብረ ብርሃን ከተማ ስራ…

ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ ከጆ ባይደን ጋር ያደረጉት የስልክ ውይይት በዲፕሎማሲው አውድ መሻሻሎች የመኖራቸው ማሳያ ነው- የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

አዲስ አበባ፣ ጥር 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ጋር ያደረጉት የስልክ ውይይት ከዚህ ቀደም የነበረው የግንኙነት መንፈስ እየተቀየረ ለመሆኑ ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለፀ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ…

በምስራቅ መስቃን ቤተ ጉራጌ እና በማረቆ ወረዳ ማህበረሰብ መካከል የእርቅ ስነ ስርዓት እየተካሔደ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥር 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ ክልል በጉራጌ ዞን በምስራቅ መስቃን ቤተ ጉራጌ እና በማረቆ ወረዳ ማህበረሰብ መካከል የተፈጠረውን የጸጥታ ችግር ለመፍታት በሁለቱም ወገን የሀገር ሽማግሌዎች የእርቅ ስነ ስርዓት እየተካሔደ ነው፡፡ በሁለቱ ህዝቦች መካከል ዘላቂ ሰላም ለማስፈን…

በመላው ዓለም እውቀትና ልምድ ባካበቱ ዳያስፖራዎቻችን ለመጠቀም በሀገር ቤት አመቺ ስርዓት መፍጠር ይገባል ተባለ

አዲስ አበበባ፣ ጥር 4፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ነጻነቱን አስከብሮ በተጽዕኖው ጠንካራ የሆነ አህጉር ለመፍጠር በምጣኔ ሀብት ለመበልጸግ ልዩ ትኩረት መስጠት እንደሚገባ ምሁራን ተናገሩ። በተለያዩ የአለም ክፍሎች በርካታ እውቀት እና ልምድ ያካበቱ የአፍሪካ ዳያስፖራዎችን በሞያዎቻቸው አገልግሎቶችን…

የስደተኞችና ከስደት ተመላሾች ጉዳይ ዋና ዳይሬክተር ተስፋሁን ጎበዛይ ከተባበሩት መንግስታት የፍልሰተኞች ድርጅት የአፍሪካ ቀንድ ዳይሬክተር ጋር መከሩ

አዲስ አበባ፣ ጥር 4፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ ስደተኞችና ከስደት ተመላሾች ጉዳይ ዋና ዳይሬክተር ተስፋሁን ጎበዛይ ከተባበሩት መንግስታት የፍልሰተኞች ድርጅት የአፍሪካ ቀንድ ዳይሬክተር ሞሃመድ አብዲከር ጋር መክረዋል፡፡ በሁለቱ ተቋማት መካከል ትብብርን ማጠናከር በሚያስችሉ ተግባራት ላይ…