Fana: At a Speed of Life!

የበጎ ፈቃደኞች ተግባር የአሁኑ ትውልድ ቅርስ ሆኖ የሚያገለግል ነው – ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል

አዲስ አበባ፣ ጥር 13፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ ሰላም ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል በጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ እየሰለጠኑ ካሉ በጎ ፈቃደኛኞች ጋር ተወያዩ። በኢፌዴሪ ሰላም ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል የተመራ ልዑክ በጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ እየሰለጠኑ ያሉ 471 በጎ ፈቃደኛኞችን…

ጎዴ እና ሃርገሌ ደም ባንኮች አገልግሎት መስጠት ጀመሩ

አዲስ አበባ፣ ጥር 12፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) በሱማሌ ክልል የሚገኙት 2 ደም ባንኮች ሙሉ ዝግጅት በመጨረስ በአቅራቢያቸው ለሚገኙ የጤና ተቋማት ደም ማድረስ መጀመራቸውን የጤና ሚኒስቴር ገለጸ። ይህም በክልሉ ያሉ የደም ባንኮችን ቁጥር 3 ያደረሰ ሲሆን የጤና ተቋማትም ደም እና የደም አቅርቦት…

ኢትዮጵያ እና ጂቡቲ የባህር-አየር ካርጎ አገልግሎት ለመጀመር ተስማሙ

አዲስ አበባ፣ ጥር 12፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና የጂቡቲ የነፃ ቀጠናና ወደብ ባለስልጣን በጋራ በመሆን የባህር-አየር ካርጎን በመጀመር የሸቀጦችን ዝውውር በማቀላጠፍ የአህጉሪቱን ንግድ ይበልጥ ማሳለጥ በሚቻልበት ዙሪያ ለመስራት ተስማምተዋል። በተለይ ከቻይና ወደ አፍሪካ…

ም/ጠ/ሚ ደመቀ መኮንን ከአሜሪካ ስቴት ዲፓርትሜንት የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ቲቦር ናዥ ጋር በስልክ ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ጥር 12፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ)የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ከአሜሪካ ስቴት ዲፓርትሜንት የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ቲቦር ናዥ ጋር በስልክ ተወያዩ። አቶ ደመቀ በሰሜን የአገራችን ክፍል ስለተካሄው የህግ ማስከበር ዘመቻ፣ በትግራይ…

ባለፉት 24 ሰዓታት 307 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል

አዲስ አበባ፣ ጥር 12፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ በተደረገ 4,085 የላቦራቶሪ ናሙና ምርመራ 307 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። ጤና ሚኒስቴር እንዳስታወቀው በአጠቃላይ በኢትዮጵያ እስካሁን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 132,034 ደርሷል። በሌላ…

በታህሳስ ወር ከ22 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ተሰበሰበ

አዲስ አበባ፣ ጥር 12፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በታህሳስ ወር ከ22 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የገቢዎች ሚኒስትር አቶ ላቀ አያሌው አስታወቁ፡፡ ሚኒስቴሩ በታህሳስ ወር 21 ቢሊየን 338 ሚሊየን 652 ሺህ 82 ብር ለመሰብሰብ አቅዶ 22 ቢሊየን 375 ሚሊየን 335 ሺህ 266 ብር ገቢ…

351 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ሲገኝባቸው 188 ሰዎች አገግመዋል

አዲስ አበባ፣ ጥር 10፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) ባለፉት 24 ሰዓታት በተደረገ 4 ሺህ 980 የላቦራቶሪ ምርመራ 351 ሰዎች ኮሮናቫይረስ እንደተገኘባቸው ተረጋግጧል። በአጠቃላይ እስካሁን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 131 ሺህ 546 ደርሷል። በሌላ በኩል 188 ሰዎች ከቫይረሱ ያገገሙ ሲሆን…

የብሔራዊ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን በትግራይ ክልል ለሽሬ እና አካባቢው ነዋሪዎች አልሚ ምግብና መድሃኒት ላከ

አዲስ አበባ፣ ጥር 10፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የብሔራዊ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን በትግራይ ክልል ለሽሬ እና አካባቢው ነዋሪዎች 500 ኩንታል አልሚ ምግብና መድሃኒት ድጋፍ ወደ ስፍራው መላኩ ተገለጸ፡፡ ኮሚሽኑ አልሚ ምግቦቹ እና መድሃኒቶቹ በፍጥነት ወደ ስፍራው እንዲደርሱ በማሰብ…

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሕወሃትን ህጋዊ ሰውነት መሰረዙን አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ ጥር 10፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ)የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ ላይ ዛሬ ባስተላለፈው ውሳኔ የሕወሃትን ህጋዊ ሰውነት መሰረዙን አስታውቋል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በህግ ከተቋቋመባቸው ዋና ዋና ተግባራት አንዱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ድጋፍ፥ ቁጥጥር እና…

በደቡብ ክልል በ147 ሚሊየን ብር በጀት 7 አነስተኛ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ ውል ስምምነት ተፈረመ

አዲስ አበባ፣ ጥር 10፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ)በደቡብ ክልል በ147 ሚሊየን ብር በጀት 7 አነስተኛ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ ውል ስምምነት የፊርማ ስነ ስርዓት ተካሂዷል፡፡ የደቡብ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ እንደገለጸው በክልሉ ከ2009 ጀምሮ በተሳትፏዊ አነስተኛ መስኖ ልማት…