Fana: At a Speed of Life!

ጅማ ዩኒቨርሲቲ በሀገር አቀፍ ደረጃ ትኩረት በተሰጣቸው የትምህርት ዘርፎች ምሁራንን ለማፍራት እየሰራ መሆኑን አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 10፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ጅማ ዩኒቨርሲቲ በሀገር አቀፍ ደረጃ ትኩረት በተሰጣቸው የትምህርት ዘርፎች 5 ሺህ ፒ.ኤች.ዲ ምሩቃንን ለማፍራት እየሰራ መሆኑን አስታወቀ፡፡ በምርምር፥ በሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲነት የተመረጡ 10 የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በበርካታ ዘርፎች…

አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን አና አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በውጭ ቋንቋዎች ከሚጽፉ የሚዲያ ባለሙያዎችና የማህበረሰብ አንቂዎች ጋር ውይይት አደረጉ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 10፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዲኤታና የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የመረጃ ፍሰት ቃል አቀባይ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በውጭ ቋንቋዎች ከሚጽፉ የሚዲያ ባለሙያዎችና የማህበረሰብ አንቂዎች ጋር ተወያዩ።…

ስፖርት ህዝባዊ መሠረት እንዲኖረውና ራሱን እንዲችል የከተማ አስተዳደሩ ድጋፍ ያደርጋል­- ም/ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 10፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ስፖርት ህዝባዊ መሠረት እንዲኖረው እና እራሱን ችሎ እንዲንቀሳቀስ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ተገቢውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ ገለፁ። 12ኛው የአዲስ አበባ ከተማ የስፖርት ምክር ቤት በመካሄድ ላይ ይገኛል።…

በፕሪሚየር ሊጉ ኢትዮጵያ ቡና ፋሲል ከነማን አሸነፈ

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 10 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ድል ቀንቶታል። ረፋድ ላይ በተደረገ ጨዋታ ኢትዮጵያ ቡና ፋሲል ከነማን 3 ለ 1 አሽንፏል። ታፈሰ ሰለሞን፣ አቡበክር ናስር እና ሃብታሙ ታደሰ የድል ጎሎቹን አስቆጥረዋል። በዛብህ…

ልዩ ድጋፍ የሚሹና ያልለሙ አካባቢዎችን በተሻለ መልኩ መለወጥ የሚያስችል የሦስት ዓመት ዕቅድ ይዘጋጃል – አቶ ደመቀ መኮንን

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 10፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአቅምና የልማት ክፍተት በሚታይባቸውና ልዩ ድጋፍ በሚሹ አካባቢዎች የተሻለ ልማት ለማምጣት የሦስት ዓመት ዕቅድ የሚዘጋጅ መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ገለጹ። የፌዴራል ልዩ ድጋፍ ቦርድ አባላት የቦርዱን…

የብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ ለሁለት ቀናት ሲያካሂድ የቆየውን መደበኛ ስብሰባ አጠናቀቀ

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 10 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ ለሁለት ቀናት ሲያካሂድ የቆየውን መደበኛ ስብሰባ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፈ አጠናቀቀ፡፡ ኮሚቴው በሰላም፣ በልማት፣ በዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታና መጪዉን ሃገራዊ ምርጫ በተመለከቱ አጀንዳዎች ላይ በጥልቀት…

አሜሪካ ሞደርና ክትባት ጥቅም ላይ እንዲውል ፈቃድ ሰጠች

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 10 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) አሜሪካ ሞደርና የኮቪድ 19 ክትባት ጥቅም ላይ እንዲውል ፈቃድ ሰጠች፡፡ የሃገሪቱ የምግብ መድሃኒት እና ቁጥጥር ባለስልጣን የሞደርና ክትባት በአሜሪካ ሁለተኛው ክትባት ሆኖ ያገለግል ዘንድ እውቅና ሰጥቷል፡፡ ባለስልጣኑ ከሳምንት በፊት…

የብሔራዊ ስታዲየም የጣራ መሸከሚያ ምሰሶ ኮንክሪት ሙሌት ተጀመረ

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 10 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የብሔራዊ ስታዲየም የጣራ መሸከሚያ ምሰሶ ኮንክሪት ሙሌት ተጀመረ። የስታዲየሙ ሁለተኛው እና የማጠቃለያ ምዕራፍ ግንባታ የፊርማ ስነ ስርአት በዛሬው እለት ተካሄዷል፡፡ በዚህ ወቅትም የፕሮጀክቱ የሁለተኛ ምዕራፍ ስራው ዋና አካል የሆነው…

በቡራዩ በደረሰ የእሳት አደጋ ግምቱ 10 ሚሊየን ብር የሆነ ንብረት መውደሙ ተገለፀ

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 10፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በቡራዩ ከተማ በደረሰ የእሳት አደጋ ግምቱ 10 ሚሊየን ብር የሆነ ንብረት መውደሙ ተገለፀ፡፡ ትናንት ከቀኑ 8 ሰዓት አካባቢ በደረሰው የእሳት አደጋ ግምቱ 10 ሚሊየን ብር የሆነ ንብረት መውደሙን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳድር የእሳት እና…

የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹን አስመረቀ

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 10፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ መርሐግብሮች ሲያስተምራቸው የነበሩ ተማሪዎቹን አስመረቀ፡፡ ዩኒቨርሲቲው በዛሬው እለት ያስመረቃቸው ተማሪዎች ቁጥር 1 ሺህ 300 ተማሪዎች ናቸው፡፡ ከዚህ ውስጥ 1 ሺህ 228 በመጀመሪያ ዲግሪ…