Fana: At a Speed of Life!

አቶ እስክንድር ነጋን ጨምሮ በ7 ግለሰቦች ላይ አቃቤ ህግ ያቀረበውን ክስ እንዲያሻሽል ፍርድ ቤቱ ትእዛዝ ሰጠ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 12፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ፍርድ ቤቱ አቶ እስክንድር ነጋን ጨምሮ በ7 ግለሰቦች ላይ አቃቤ ህግ ያቀረበውን ክስ እንዲያሻሽል ትእዛዝ ሰጥቷል። የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አንደኛ የሕገ መንግስት እና የፀረ ሽብር ወንጀል ችሎት አቃቤ ህግ ከዚህ በፊት…

ብልፅግና ፓርቲ በሩሲያ ገዢ ፓርቲ አዘጋጅነት በተካሄደው የኢንተርኔት ኮንፈረንስ ላይ ተሳተፈ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 11፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የሩሲያ ገዢ ፓርቲ ብልፅግናን ጨምሮ ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ገዢ ፓርቲዎች ጋር የኢንተርኔት ኮንፈረንስ አካሄደ። በሩሲያው "ዩናይትድ ሩሲያ" ፓርቲ አዘጋጅነት የተዘጋጀው ይህ ኮንፈረንስ የኢትዮጵያው ብልፅግና፣ የደቡብ አፍሪካ ኤ.…

የግብርና ሚኒስትር አቶ ዑመር ሁሴንን ጨምሮ የፋኦ የኢትዮጵያ ተወካይ በአፋር ክልል የበረሃ አንበጣ ያለበትን ሁኔታ ተመለከቱ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 11፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የግብርና ሚኒስትር አቶ ዑመር ሁሴን ፣ ሚኒስትር ዴኤታ ማንደፍሮ ንጉሴን እና የዓለም የምግብ እና እርሻ ድርጅት (ፋኦ) የኢትዮጵያ ተወካዮች በአፋር ክልል የበረሃ አንበጣ ያለበትን ሁኔታ እና እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎችን ተመልክተዋል። በጉብኝቱ…

እነ አቶ ጃዋር መሀመድ፣ በቀለ ገርባና ሀምዛ አዳነን ጨምሮ 18 ግለሰቦች ፍርድ ቤት ቀርበው ክስ ተመሰረተባቸው

አዲስ አበባ፣ መስከረም 11፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) እነ አቶ ጃዋር መሀመድ፣ በቀለ ገርባና ሀምዛ አዳነን ጨምሮ 18 ግለሰቦች ፍርድ ቤት ቀርበው ክስ ተመስርቶባቸዋል። ተከሳሾቹ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 1ኛ ህገ መንግስትና ጸረ ሽብር ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ቀርበው ክሱ ደርሷቸዋል።…

በግብፅ ፕሬዚዳንት አብዱል ፈታህ አል ሲሲ ላይ ተቃውሞ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ መስከረም 11፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በግብፅ ጋዛ ግዛት የአብዱል ፈታህ አል ሲሲ መንግስትን የሚቃወሙ ሰልፎች እየተካሄዱ መሆኑ ተነገረ። መንግስትን በመቃወም ሰልፍ እየተካሄደባቸው በሚገኙ አካባቢዎች ከፍተኛ የፀጥታ ቁጥጥር እንዳለ አልጀዚራ ዘግቧል። በማህበራዊ መገናኛ ብዙሃን…

የቢሾፍቱ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ለአገልግሎት ዝግጁ ሆነ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 11 ፣ 2013(ኤፍ.ቢ.ሲ)ከ25 ሚሊየን ዶላር በላይ በሆነ ወጪ በቢሾፍቱ ከተማ የተገነባው ባለ 400/230/15 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታው ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል አስታወቀ። የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ…

የሱልጣን ሀንፍሬ አሊሚራህ የቀብር ስነ ስርዓት ተፈፀመ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 11፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በትናንትናው እለት ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት የአፋር ሱልጣን ሀንፍሬ ዓሚራህ የቀብር ስነ ስርዓት ዛሬ ተፈፅሟል፡፡ ስርዓተ ቀብራቸው በአሳይታ ከተማ የተፈፀመ ሲሆን በስርዓተ ቀብር ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ…

ከአዲስ አበባ ወደ ባንኮክ ሊጓጓዝ የነበረ አራት ኪሎ ግራም ኮኬይን በቁጥጥር ሥር ዋለ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 9፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ወደ ታይላንድ ዋና ከተማ ባንኮክ ሊጓጓዝ የነበረ 400 ሺህ ዶላር የሚያወጣ 4 ኪሎ ግራም ኮኬይን በአዲስ አበባ ቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በቁጥጥር ሥር ማዋሉን የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት አስታወቀ። አገልግሎቱ ለፋና…

ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ በተደረገ የላቦራቶሪ ናሙና ምርመራ 616 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል

አዲስ አበባ፣ መስከረም 9፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ በተደረገ 10 ሺህ 322 የላቦራቶሪ ናሙና ምርመራ 616 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው መረጋገጡን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።   በአጠቃላይ እስካሁን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 68 ሺህ 131 ደርሷል።…