Fana: At a Speed of Life!

መኪና አስመጣላሁ በሚል ከ17 ሚሊየን ብር በላይ ከሰዎች ሰብስቦ ተሰወረ የተባለው ኩባንያ ምላሽ ሰጥቷል

አዲስ አበባ፣ ጥር 28፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) መኪና አስመጣላሁ በሚል ከግለሰብ 173 ሺህ ብር በላይ በድምሩ ከ17 ሚሊየን ብር በላይ ሰብስቦ ተሰወረ የተባለው ኩባንያ አለሁ ብሏል። ፋት ትራንስፖርት ቴክኖሎጂስ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር አሽከርካሪውን ጨምሮ 5 ሰዎችን የሚያሳፍር መኪና፣…

እስራኤል በሶሪያ ደማስቆ አቅራቢያ በኢራን የሚደገፉ ሀይሎች ላይ የአየር ጥቃት ፈፀመች

አዲስ አበባ፣ ጥር 28፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) እስራኤል በሶሪያ ደማስቆ አካባቢ በሚንቀሳቀሰው እና በኢራን በሚደገፈው ሀይል ላይ እርምጃ መውሰዷ ተገለፀ። ሳና የዜና አገልግሎት እንዳስነበበው ከእስራኤል የተተኮሱ በርካታ ሚሳኤሎችን መመከት ቢቻልም፤ ስምንት ሰዎች ላይ ግን ጉዳት ደርሷል ብሏል።…

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ከተለያዩ ሀገራት ልዩ መልዕክተኞች ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ጥር 28፣2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ከ36ኛው የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚዎች ምክር ቤት ስብሰባ ጎን ለጎን ከተለያዩ ሀገራት ልዩ መልዕክተኞች ጋር ተወያይተዋል። ሚኒስትሩ ከአየርላንድ መንግስት ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ኬኔት ቶምሰን እና…

የአማራ ግብርና ምርምር ኢንስቲቲዩት የአፍሪካ ኦስትሪያ የምርምር ጥምረት አባል ሆነ

አዲስ አበባ፣ ጥር 28 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የአማራ ግብርና ምርምር ኢንስቲቲዩት የአፍሪካ ኦስትሪያ የምርምር ጥምረት አባል መሆኑ ተገለጸ። የአማራ ግብርና ምርምር በኦስትሪያ መንግስት የሳይንስና ትምህርት ሚኒስቴር ድጋፍ የተመሰረተው የአፍሪካ ኦስትሪያ የምርምር ጥምረት መረብ አባል ሆኗል።…

ለጋሾች በየመን በሃውቲ ቁጥጥር ስር በሚገኙ ይዞታዎች የሚያደርጉትን ሰብአዊ እርዳታ እንደሚቀንሱ ገለጹ

አዲስ አበባ፣ ጥር 28፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ለጋሾች በየመን በሃውቲ አማጽያን ቁጥጥር ስር በሚገኙ ይዞታዎች የሚያደርጉትን ሰብዓዊ ድጋፍ ሊቀንሱ እንደሚችሉ አስታወቁ። ለዚህም በአካባቢው ያለው ሁኔታ ለስራቸው እንቅፋት መሆኑን ገልጸዋል። በአካባቢው ባለው ወቅታዊ ሁኔታ ሳቢያም ሰብዓዊ ድጋፉ…

ቋሚ ኮሚቴው በፍርድ ቤቶች የቀጠሮ መራዘም ችግር እንዳለ ገለፀ

አዲስ አበባ፣ ጥር 28፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግ፣ ፍትህ እና ዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በፍርድ ቤቶች የቀጠሮ መራዘም ችግር መኖሩን ገለፀ። ቋሚ ኮሚቴው በጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት እና የከፍተኛ ፍርድ ቤቶች ያደረገውን የመስክ…

በአማራ ክልል በ20 ሚሊየን ብር ወጪ የተገነባው የዓሳ ጫጩት ማስፈልፈያ ማዕከል ሙሉ በሙሉ ወደ ስራ ሊገባ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥር 28፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በ20 ሚሊየን ብር ወጪ የተገነባው የአሳ ጫጩት ማስፈልፈያ ማዕከል ሙሉ በሙሉ ወደ ስራ ሊገባ መሆኑን የአማራ ክልል ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት አስታወቀ። የክልሉ የባህር የአሳ እና ሌሎች የውሃ ውስጥ አካላት ምርምር ዳይሬክተር አቶ ደረጀ ተዋበ…

በግድቡ ዙሪያ የሚደረጉ ድርድሮች ሁሉንም ወገን ተጠቃሚ በሚያደርግ ስምምነት ላይ ትኩረት ማድረግ ይገባቸዋል- ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ

አዲስ አበባ፣ ጥር 28፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ የሚደረጉ ድርድሮች ሁሉንም ወገን ተጠቃሚ በሚያደርግ ስምምነት ላይ ትኩረት ማድረግ እንደሚገባቸው የውሃ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ገለፁ። የስትራቴጂክ ጉዳዮች ተቋም የሚያዘጋጀው…