Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

የአርሰናል የቀድሞ ተጫዋች ሳንቲ ካዞርላ ራሱን ከእግር ኳስ ዓለም አገለለ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ስፔናዊው የአርሰናል የቀድሞ ተጫዋች ሳንቲ ካዞርላ ራሱን ከእግር ኳስ ዓለም ማግለሉን ይፋ አድርጓል፡፡ የመድፈኞቹ የቀድሞ ተጫዋች ሳንቲ ካዞርላ በ41 ዓመቱ ጫማውን መስቀሉን በማህበራዊ ትስስር ገጹ አስፍሯል፡፡ ተጫዋቹ ያለፉትን ሦስት የውድድር ዓመታት በልጅነት ክለቡ ሪያል ኦቬዶ ማሳለፉ ይታወሳል፡፡ ሳንቲ ካዞርላ በተጨዋችነት ዘመኑ ለአርሰናል፣ ቪያሪያል፣ ማላጋ እና አል ሳድ ለመሳሰሉ ክለቦች ተጫውቶ አሳልፏል፡፡
Read More...

ፖርቹጋል ከክሮሺያ ፤ ስፔን ከኦስትሪያ…

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ እየተካሄደ በሚገኘው 23ኛው የዓለም ዋንጫ የ32ቱ ጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ዛሬም ቀጥለው ይደረጋሉ፡፡ በዚህ መሰረትም የአንድ ጊዜ የመድረኩ ሻምፒዮን ስፔን ምሽት 4 ሰዓት ላይ ከኦስትሪያ ጋር ጨዋታዋን ታደርጋለች፡፡ ምድቧን በበላይነት እየመራች ጥሎ ማለፉን የተቀላቀለችው ስፔን ለዋንጫው ቅድመ…

እንግሊዝ ዲሞክራቲክ ኮንጎን በማሸነፍ 16ቱን ተቀላቀለች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ እንግሊዝ ዲሞክራቲክ ኮንጎን 2 ለ 1 በማሸነፍ 16ቱን ተቀላቅላለች። ምሽት 1 ሰዓት ላይ በአትላንታ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የእንግሊዝን የማሸነፊያ ግቦች ሃሪ ኬን አስቆጥሯል፡፡ ዲሞክራቲክ ኮንጎ በጨዋታው ጥሩ እንቅስቃሴ በማድረግ እንዲሁም አስቀድማ ግብ…

ቼልሲ ጣሊያናዊውን ተከላካይ ማርኮ ፓሌስትራን አስፈረመ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ቼልሲ ጣሊያናዊውን የአታላንታ የክንፍ ተከላካይ ማርኮ ፓሌስትራን አስፈርሟል፡፡ የ21 አመቱ ፓሌስትራ የዣቪ አሎንሶ የመጀመሪያ ፈራሚ በመሆን ስታንፎርድ ብሪጅ የደረሰ ሲሆን፤ በ47 ሚሊየን ፓውንድ የዝውውር ዋጋ ቼልሲን ተቀላቅሏል። ተጨዋቹ ለስድስት ዓመታት በምዕራብ ለንደኑ ክለብ ለመቆየትም ኮንትራት ፈርሟል፡፡…

መቐለ 70 እንደርታ እና ድሬዳዋ ከተማ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 38ኛ ሳምንት የጨዋታ መርሐ ግብር መቐለ 70 እንደርታ ነገሌ አርሲን 3 ለ 0 አሸንፏል። በዛሬው ዕለት ቀን 9 ሰዓት ላይ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተካሄደ ጨዋታ የመቐለ 70 እንደርታን ግቦች መሃሪ አምሃ፣ ብርሃኑ አዳሙ እና ፍሬዘር ካሳ አስቆጥረዋል። እንዲሁም በተመሳሳይ ሰዓት በአዳማ…

እንግሊዝ ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ፤ ቤልጂዬም ከሴኔጋል…

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ እየተካሄደ በሚገኘው 23ኛው የዓለም ዋንጫ የ32 ጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ዛሬም ቀጥለው ይካሄዳሉ፡፡ በዚህ መሰረትም የአፍሪካ አህጉር ተወካዮቹ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና ሴኔጋል 16ቱን ለመቀላቀል የሚፋለሙ ይሆናል፡፡ ምሽት 1 ሰዓት ላይ እንግሊዝ እና ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ…

ፓራጓይ በዓለም ዋንጫ ጀርመንን ያሸነፈችበትን ቀን ብሔራዊ በዓል እንዲሆን አወጀች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫ የ32ቱ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ፓራጓይ የ4 ጊዜ የመድረኩን ባለክብር ጀርመን ሳትጠበቅ በማሸነፍ 16ቱን መቀላቀል ችላለች፡፡ ደቡብ አሜሪካዊቷ ሀገር ትናንት ምሽት ጀርመንን በመለያ ምት 4 ለ 3 በማሸነፍ ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፏ ይታወቃል፡፡ ድሉን ተከትሎ የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ሳንቲያጎ ፔና የዛሬው ዕለት የፓራጓይ…