Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

ድሬዳዋ ከተማ በፕሪሚየር ሊጉ መቆየቱን አረጋገጠ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ድሬዳዋ ከተማ ስሑል ሽረን በማሸነፍ በሊጉ መቆየቱን አረጋግጧል፡፡ በ35ኛ ሳምንት የሊጉ መርሐ ግብር በወንጂ ሁለገብ ስታዲየም ከሊጉ መውረዱን ያረጋገጠውን ስሑል ሽረን የገጠመው ድሬዳዋ ከተማ 4 ለ 2 አሸንፏል፡፡ የድሬዳዋ ከተማን የማሸነፊያ ግቦች መስዑድ መሐመድ (2) እንዲሁም ዮሀንስ ደረጀ እና ሀቢብ ከማል አስቆጥረዋል፡፡ የስሑል ሽረን ግቦች ብርሃኑ አዳሙ እና አላዛር ሽመልስ ከመረብ አሳርፈዋል፡፡ ውጤቱን ተከትሎ ድሬዳዋ ከተማ ነጥቡን 43 በማድረስ…
Read More...

ሲዳማ ቡና እና አርባ ምንጭ ከተማ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ሲዳማ ቡና እና አርባ ምንጭ ከተማ ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይተዋል። ረፋድ 3፡30 ላይ በወንጂ ሁለገብ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ነው ሁለቱ ቡድኖች 0 ለ 0 በሆነ አቻ ውጤት የተለያዩት። የሊጉ መርሐ ግብር ሲቀጥል ቀን 9 ሰዓት ባህር ዳር ከተማ እና ሀዋሳ ከተማ…

ፋሲል ከነማ እና አዳማ ከተማ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 35ኛ ሳምንት መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት ሶስት ጨዋታዎች ተካሂደዋል፡፡ በሊጉ ላለመውረድ በሚደረገው ፉክክር ውስጥ የሚገኙ ቡድኖች የተሳተፉባቸው ሦስት ጨዋታዎች በተመሳሳይ 9 ሰዓት ላይ ነው የተካሄዱት፡፡ በዚህ መሰረትም አዳማ ከተማ እና ፋሲል ከነማ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም…

የክለቦች የዓለም ዋንጫ …

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የተሳታፊ ክለቦችን ቁጥር ወደ 32 ከፍ በማድረግ ዳጎስ ያለ ሽልማት ይዞ በአዲስ የውድድር ቅርጽ የተመለሰው የክለቦች የዓለም ዋንጫ ዛሬ ሌሊት ይጀምራል፡፡ በአሜሪካ በተሰናዳው የክለቦች ዓለም ዋንጫ 12 የአውሮፓ ክለቦችን ጨምሮ ከሁሉም አህጉራት በአጠቃላይ 32 ክለቦች ተሳታፊ ይሆናሉ፡፡ በፈረንጆቹ 2000 የተጀመረው የፊፋ…

ኢትዮጵያ ቡና ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ኢትዮጵያ ቡና ቅዱስ ጊዮርጊስን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ የኢትዮጵያ ቡናን የማሸነፊያ ግቦች ዲቫይን ዋቹኩዋ እና አማኑኤል አድማሱ አስቆጥረዋል፡፡ ውጤቱን ተከትሎ ኢትዮጵያ ቡና በ59 ነጥብ 2ኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ ቅዱስ ጊዮርጊስ በ45 ነጥብ 7ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡…

ሪያል ማድሪድ የራውል አሴንሲዮን ውል አራዘመ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ሪያል ማድሪድ የስፔናዊውን የተከላካይ ስፍራ ተጫዋች ራውል አሴንሲዮ ከክለቡ ጋር ያለውን ውል እስከ የፈረንጆቹ 2031 ድረስ አራዝሟል፡፡ የ22 ዓመቱ የተከላካይ ስፍራ ተጫዋች ራውል አሴንሲዮ በሪያል ማድሪድ እስከ 2029 የሚያቆይ ኮንትራት ቢኖረውም ለተጨማሪ ሁለት ዓመታት ለመቆየት ተስማምቷል፡፡ ሪያል ማድሪድ የተከላካይ…

ጀግናው አትሌት ቀነኒሳ በቀለ …

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 6፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በርካታ ጀግና ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በዓለም ላይ በሚያደርጓቸው ውድድሮችና በሚያመጧቸው ውጤቶች የሀገራቸውን ህዝብ በደስታ ዕንባ አራጭተዋል፤ ስሜትን ከፍ ዝቅ የሚያደርጉ በርካታ አኩሪ ገድሎችንም ሰርተዋል፤ እየሰሩም ይገኛሉ። ነገር ግን እርሱ ከሁሉም ልዩ ነው ትውልድ ከትውልድ የሚቀባበላቸው ዘመን ተሻጋሪ የጀግንነት እና…