ስፓርት
ድርቤ ወልተጂ በአንድ ማይል የሴቶች የጎዳና ላይ ሩጫ ሪከርድ ሰበረች
አዲስ አበባ፣ መስከረም 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) አትሌት ድርቤ ወልተጂ በአንድ ማይል የሴቶች የጎዳና ላይ ሩጫ ሪከርድ በመስበር አሸነፈች፡፡
ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሴቶች አንድ ማይል የሪጋ የዓለም የጎዳና ላይ ሩጫ ድል ቀንቷቸዋል፡፡
ርቀቱን አትሌት ድርቤ ወልተጂ በቀዳሚነት ስታጠናቅቅ ፍሬወይኒ ኃይሉ ደግሞ ሁለተኛ ደረጃን ይዛለች፡፡
ድርቤ ወልተጂ በ4 ደቂቃ ከ21 ሰከንድ በሆነም ነው የዓለምን ሪከርድ የሰበረችው፡፡
ሁለተኛ የወጣችው ፍሬወይኒ ኃይሉ 4 ደቂቃ ከ23 ሰከንድ ከ6ሚሊ ሰከንድ በሆነ 2ኛ መውጣቷን ከአትሌቲክስ…
Read More...
ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በ5 ኪሎ ሜትር የዓለም የጎዳና ላይ ሩጫ ድል ቀናቸው
አዲስ አበባ፣ መስከረም 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በወንዶች 5 ኪሎ ሜትር የሪጋ የዓለም የጎዳና ላይ ሩጫ ድል ቀንቷቸዋል፡፡
አትሌት ሀጐስ ገ/ሕይወ ርቀቱን 12 ደቂቃ ከ59 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በማጠናቀቅ ቀዳሚ መሆን ችሏል፡፡
ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ ደግሞ ርቀቱን በ13 ደቂቃ ከ02 ሰከንድ በማጠናቀቅ 2ኛ ደረጃን ይዟል፡፡…
ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የሚጠበቁበት የሪጋ የዓለም የጎዳና ላይ ሩጫ ተካሄደ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የሚጠበቁበት በላቲቪያ ሪጋ የሚሄደው የዓለም የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር ተካሂዷል፡፡
ኢትዮጵያ በሻምፒዮናው በሰባት ሴቶች እና በስድስት ወንዶች በድምሩ በ13 አትሌቶች ተወከላለች።
በሴቶች የ5 ኪሎ ሜትር ውድድር እጅጋየሁ ታዬ እና መዲና ኢሳ ከቀኑ 5፡50 ላይ ውድድራቸውን አድርገዋል፡፡ በዚሁ…
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሁለቱ የማንቼስተር ከተማ ክለቦች ሲሸነፉ አርሰናል ድል ቀንቶታል
አዲስ አበባ ፣ መስከረም 19 ፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 7ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ሁለቱ የማንቼስተር ከተማ ክለቦች ተሸንፈዋል።
ከቀትር በኋላ በተካሄደ ጨዋታ አስቶንቪላ ብራይተንን 6 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
በተመሳሳይ 11 ሰአት ላይ በተደረጉ ጨዋታዎች ደግሞ የፕሪሚየር ሊጉ መሪ ማንቼስተር ሲቲ በወልቨርሃምፕተን ወንደረርስ…
በሪጋ በሚካሄደው የዓለም የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድር ኢትዮጵያውን አትሌቶች ይጠበቃሉ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 19፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ለመጀመሪያ ጊዜ በሦስት ርቀቶች በላቲቪያ ሪጋ ነገ በሚካሄደው የዓለም የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይጠበቃሉ፡፡
5፡50 ላይ በሚካሄደው የ5 ኪሎ ሜትር የሴቶች ውድድር አትሌት እጅጋየሁ ታዬ እና መዲና ኢሳ ሲሳተፉ÷ በዚሁ ርቀት 12፡15 ላይ በሚካሄደው የወንዶች ውድድር አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ እና ሀጐስ…
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ነገ ይጀመራል
አዲስ አበባ፣ መስከረም 19፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የ2016 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ነገ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ የኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጀመራል፡፡
ፕሪሚየር ሊጉ አዳማ ከተማ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 9፡00 ላይ በሚያደርጉት ጨዋታ ነው የሚጀመረው፡፡
የነገው የጨዋታ መርሐ- ግብር ሲቀጥል 12፡00 ላይ ሲዳማ ቡና ከኢትዮጵያ ቡና ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
በበርሊን የሴቶች ማራቶን ክብረወሰን ለሰበረችው አትሌት ትዕግስት አቀባበል ተደረገላት
አዲስ አበባ፣ መስከረም 18፣2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ49ኛው የበርሊን ሴቶች ማራቶን የዓለም ክብረወሰንን በማሻሻል ላሸነፈችው አትሌት ትዕግስት አሰፋ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ አቀባበል ተደርጎላታል።
አትሌቷ ዛሬ ማለዳ አዲስ አበባ ስትገባ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴዔታ አምባሳደር መስፍን ቸርነትና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ረዳት ኮሚሽነር…