ስፓርት
ተጠባቂው የማንቼስተር ሲቲ እና የሊቨርፑል ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቀቀ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 15፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 13ኛ ሳምንት ተጠባቂው የማንቼስተር ሲቲ እና የሊቨርፑል ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቅቋል፡፡
በኢትሃድ የተደረገው የሁለቱ ተፎካካሪ ቡድኖች ጨዋታ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቅቋል፡፡
የማንቼስተር ሲቲን ጎል ኤርሊንግ ሃላንድ በ27ኛው ደቂቃ ሲያስቆጥር ሊቨርፑልን አቻ ያደረገችውን ጎል ደግሞ ትሬንት አሌክሳንደር አርኖልድ በ80ኛው ደቂቃ በስሙ አስመዝግቧል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦…
Read More...
የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በወሳኝ ጨዋታዎች ዛሬ ይመለሳል
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 15፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ከዓለም አቀፍ ጨዋታዎች መልስ ዛሬ ማንቼስተር ሲቲ ከሊቨርፑል በሚያደርጉት ወሳኝ ጨዋታ ይጀምራል፡፡
9፡30 ላይ በኢትሃድ በሚደረገው የሁለቱ ተፎካካሪ ቡድኖች ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ መሪነቱን ለማስጠበቅ ሊቨርፑል ደግሞ አሸንፎ መሪነቱን ለመረከብ ይፋለማሉ፡፡
የሊቨርፑሉ አሰልጣኝ የርገን ክሎፕ÷ ዛሬ…
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አትሌቲክስ ክለብ የ18ኛው የኢትዮጵያ ማራቶን ሪሌ ውድድርን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 15፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አትሌቲክስ ክለብ የ18 ኛውን የኢትዮጵያ ማራቶን ሪሌ ውድድር በማሸነፍ የወርቅ ሜዳሊያና የገንዘብ ተሸላሚ ሆኗል፡፡
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን 19 ኛውን የኢትዮጵያ ማራቶን ሪሌ ውድድር በትግራይ ክልል መቀሌ ከተማ አካሂዷል፡፡
መነሻና መድረሻውን ሰማዕታት ሐውልት በማድረግ ነው በሁለቱም ጾታዎች…
19ኛው የኢትዮጵያ ማራቶን ሪሌ ውድድር በመቀሌ እየተካሄደ ነው
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 15፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) 19ኛው የኢትዮጵያ ማራቶን ሪሌ ውድድር በመቀሌ ከተማ መካሄድ ጀምሯል፡፡
በውድድሩ ከዘጠኝ ክለቦች፣ ሥድስት ክልሎችና ከተማ መሥተዳደሮች የተውጣጡ 84 አትሌቶች እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡
በሁለቱም ጾታዎች 1ኛ ለሚወጡ አትሌቶች ለእያንዳንዳቸው የ40 ሺህ ብር፣ 2ኛ ለሚወጡ 20 ሺህ ብር እንዲሁም 3ኛ ለሚወጡት የ15 ሺህ ብር…
19ኛው የኢትዮጵያ ማራቶን ሪሌ ውድድር ነገ በመቐለ ይካሄዳል
አዲስ አበባ ፣ ሕዳር 14 ፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) 19ኛው የኢትዮጵያ ማራቶን ሪሌ ውድድር በነገው እለት በትግራይ ክልል መቐለ ይካሄዳል።
በውድድሩ ከስምንት ክለቦች፣ አምስት ክልሎችና ከከተማ መስተዳደሮች የተውጣጡ 84 አትሌቶች ይካፈላሉ።
የማራቶን ሪሌ ውድድር ስድስት አትሌቶች ከአንድ ክለብ ወይም ክልል የሚሳተፉበት የውድድር ዓይነት…
አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ በ5 ሺህ ሜትር ሴቶች ሩጫ የሰበረችው ክብረወሰን ፀደቀ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 13፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ በ5 ሺህ ሜትር ሴቶች ሩጫ የሰበረችው ክብረወሰን መጽደቁ ተነገረ፡፡
በአሜሪካ ኢውጅን በተካሄደው የዳይመንድ ሊግ ውድድር ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ የዓለምን ክብረ ወሰን በመስበር ማሸነፏ ይታወሳል።
አትሌቷ በ5 ሺህ ሜትር ሴቶች ሩጫ 14 ደቂቃ ከ00 ሴኮንድ ከ21 ማይክሮ ሴኮንድ በመግባት…
ሀድያ ሆሳዕና የአዲስ አበባ ከተማ ዋንጫ አሸናፊ ሆነ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ሀድያ ሆሳዕና ኢትዮጵያ ቡናን በመለያ ምት በማሸነፍ የ17ኛው የአዲስ አበባ ከተማ ዋንጫ አሸናፊ ሆኗል፡፡
ሀድያ ሆሳዕናን እና ኢትዮጵያ ቡናን ያገናኘው የ17ኛው የአዲስ አበባ ከተማ ዋንጫ ጨዋታ መደበኛው ሰዓት 2 አቻ የተጠናቀቀ ሲሆን በተሰጠው መለያ ምት ነብሮቹ 5 ለ 4 አሸንፈዋል፡፡
በዚህም 17ኛው የአዲስ አበባ…