ስፓርት
በማድሪድ የ10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ውድድር ጥሩነሽ ዲባባ 3ኛ ስትወጣ ዳዊት ወልዴ በቀደሚነት አጠናቀቀ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 25፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በስፔን ማድሪድ በተካሄደው የ10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ውድድር በሴቶች አንጋፋዋ አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ 3ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቃለች።
በወንዶች ደግሞ ዳዊት ወልዴ በቀዳሚነት አጠናቋል፡፡
ጥሩነሽ 10 ኪሎ ሜትሩን በ30 ደቂቃ ከ03 ሴኮንድ በመጨረስ ነው 3ኛ ደረጃን ይዛ ያጠናቀቀችው፡፡
በወንዶች የ10 ኪሎ ሜትር ውድድር ደግሞ ዳዊት ወልዴ 26 ደቂቃ ከ55 ሴኮንድ በመግባት ሲያሸንፍ ኬንያዊው አትሌት ቪንሴንት ኪማዮ 2ኛ ኡጋንዳዊው ማርቲን ኪፕሮቲች ደግሞ 3ኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል፡፡
Read More...
የሻምፒዮንስ ሊጉ የፍጻሜ ጨዋታ ነገ ምሽት በዌምብሌይ ስታዲየም ይደረጋል
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የ2023/24 አውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ ነገ ምሽት በእንግሊዙ ዌምብሌይ ስታዲየም ይደረጋል፡፡
ምሽት 4 ሰዓት ላይ ሊደረግ ቀጠሮ በተያዘለት ታላቁ የፍጻሜ ጨዋታ የአውሮፓ ሻምፒዮንሰ ሊግ ንጉሶቹ ሪያል ማድሪድ እና የጀርመኑ ክለብ ቦሩሲያ ዶርትሙንድ የባለ ትልቁ ጆሮ ዋንጫ ለማንሳት ይፋለማሉ፡፡
በጨዋታው ሎስ…
ሐጎስ ገብረህይወት በ5 ሺህ ሜትር የሩጫ ውድድር አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 22፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያዊው አትሌት ሐጎስ ገብረህይወት በዳይመንድ ሊግ የ5 ሺህ ሜትር የወንዶች ሩጫ ውድድር አሸንፏል፡፡
በውድድሩ 12፡36፡73 ሰዓት በመግባት ሲያሸንፍ ፥ በ5ሺህ ሜትር ሩጫ ውድድር ሪከርድ ለመስበር በሁለት ሰከንድ ዘግይቶ መግባቱ ተገልጿል፡፡
አትሌቱ በተሳተፈበት በዚህ ውድድርም በታሪክ የምንጊዜም ሁለተኛውን ፈጣን…
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አዲስ የትጥቅ ብራንድ ይፋ አደረገ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ቱርክ ከሚገኝ የትጥቅ አምራች ድርጅት ጋር በመተባበር “ሀገሬ” የተሰኘ የራሱን ብራንድ ማስተዋወቁን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታወቀ፡፡
የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ ጂራ እንደገለጹት÷ ፌዴሬሽኑ ከተቋሙ ጋር ያደረገው የመግዛት እና የመሸጥ ስምምነት የጊዜ ገደብ የለውም፡፡
ፌዴሬሽኑ ያስተዋወቀው የትጥቅ ብራንድ…
ቪንሴንት ኮምፓኒ የባየር ሙኒክ አሰልጣኝ ሆነ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የጀርመኑ ክለብ ባየር ሙኒክ ቤልጂየማዊውን ቪንሴንት ኮምፓኒን በአሰልጣኝነት መሾሙን አስታውቋል፡፡
ኮምፓኒ ባየር ሙኒክን በኃላፊነት የተረከበው የቀድሞው የቡድኑ አሰልጣኝ ቶማስ ቱሄል መሰናበቱን ተከትሎ ነው፡፡
በዚህም አሰልጣኝ ቪንሴንት ኮምፓኒ ባየር ሙኒክን ለሦስት የውድድር ዓመታት ለማሰልጠን እስከ 2027 የሚያቆየውን…
አትሌት ሱቱሜ አሰፋ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ቡድንን ተቀላቀለች
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) አትሌት ሱቱሜ አሰፋ በ2024ቱ የፓሪስ ኦሊምፒክ ኢትዮጵያን በመወከል የሚሳተፈው የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ቡድን ስብስብ ውስጥ ተካተች፡፡
አትሌቷ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ግንቦት 8 በፓሪስ ኦሊምፒክ ኢትዮጵያን በማራቶን የሚወክሉ አትሌቶችን ስም ዝርዝር ይፋ ሲያደርግ ሳትካተት መቅረቷ ይታወሳል።
ይህንን ተከትሎ አትሌቷ…
በኦታዋ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታዎች አሸነፉ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 18፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦታዋ በተካሄደው የማራቶን ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታዎች ድል ቀንቷቸዋል፡፡
በወንዶች ማራቶን ሌንጮ ተስፋዬ ርቀቱን 2 ሰዓት 12 ደቂቃ ከ41 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በማጠናቀቅ ቀዳሚ ሆኗል፡፡
ሌላኛው አትሌት አዳሙ ጌታሁን ደግሞ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቅቋል፡፡
በተመሳሳይ በሴቶች…