ስፓርት
ዛሬ ፍጻሜውን በሚያገኘው የአትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያውያን የሚጠበቁባቸው ሶስት ውድድሮች ይካሄዳሉ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 25፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በፔሩ ሊማ ሲካሄድ በነበረውና ዛሬ ምሽት ፍጻሜውን በሚያገኘው የዓለም ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የሚጠበቁባቸው ሶስት ውድድሮች ይካሄዳሉ።
በዚህም በ1 ሺህ 500 ሜትር ሴቶች የፍፃሜ ውድድር አትሌት ሳሮን በርሀ እና ፅጌ ተሾመ ሌሊት 7:00 ላይ ለሜዳሊያ ብርቱ ፉክክር ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
እንዲሁም በወንዶች 3 ሺህ መሰናክል የፍፃሜ ውድድር አትሌት ሃይሉ አያሌው እና በሪሁን ሞገስ ሌሊት 7:15 ላይ ውድድራቸውን ያካሂዳሉ።
የወንዶች 1 ሺህ 500…
Read More...
ከ20 ዓመት በታች የዓለም ሻምፒዮና ኢትዮጵያ የምትሳተፍባቸው 4 የፍጻሜ ውድድሮች ዛሬ ይካሄዳሉ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በፔሩ ሊማ እየተካሄደ በሚገኘው የዓለም ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የሚሳተፉባቸው አራት የፍጻሜ ውድድሮችበዛሬው ዕለት ይካሄዳሉ፡፡
በዚህ መሰረትም አትሌት ሕይወት አምባውና አትሌት ብርሃን ሙሉ የሚሳተፉበት የሴቶች 10 ሺህ ሜትር ርምጃ ውድድር ከምሽቱ 12 ሰዓት ከ25 ላይ ይካሄዳል፡፡…
አትሌት ሲምቦ ዓለማየሁ በሴቶች 3 ሺህ ሜትር መሰናክል ለኢትዮጵያ የወርቅ ሜዳሊያ አስገኘች
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በፔሩ ሊማ እየተካሄደ በሚገኘው ከ20 ዓመት በታች የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና አትሌት ሲምቦ ዓለማየሁ በሴቶች 3 ሺህ ሜትር መሰናክል ለኢትዮጵያ የወርቅ ሜዳሊያ አስገኘች።
አትሌት ሲምቦ በ9 ደቂቃ ከ12 ሰከንድ 71 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት የሻምፒዮናውን ክብረወሰን በመስበር ጭምር ነው ማሸነፍ የቻለችው፡፡
በውድድሩ ላይ…
ክርስቲያኖ ሮናልዶ የአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር ልዩ ተሸላሚ ሆነ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የምንግዜም ከፍተኛ ጎል አስቆጣሪው ክርስቲያኖ ሮናልዶ የአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር ልዩ ተሸላሚ መሆን ችሏል።
ሽልማቱ ይፋ የተደረገው ዛሬ በሞናኮ በተካሄደው የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የምድብ ድልድል ስነ ስርዓት ላይ ሲሆን፥ በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ያሳለፈው ስኬታማ ጊዜ ለሽልማቱ እንዳበቃውም…
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሻምፒዮን መሆኑን አረጋገጠ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ኬንያ ፖሊስ ቡሌትስን 1 ለ 0 በማሸነፍ የካፍ ሴቶች ሻምፒዮንስ ሊግ የሴካፋ ሀገራት ሻምፒዮን መሆኑን አረጋግጧል፡፡
ዛሬ ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተካሄደ የፍፃሜ ጨዋታ ሴናፍ ዋቁማ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን የማሸነፊያ እና ብቸኛ ግብ ከመረብ አሳርፋለች፡፡
በኢትዮጵያ…
በአውሮፓ የክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ነገ ይዘጋል
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአውሮፓ የክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ሊዘጋ ሰዓታት ሲቀረው ክለቦች ተጫዋቾችን ለማስፈረም ጥረታቸውን አጠናክረው ቀጥለዋል፡፡
የእንግሊዞቹ ክለቦች ማንቸስተር ዩናይትድ፣ ሊቨርፑል፣ አርሰናል እና ቼልሲ በመዝጊያው 11ኛ ሰዓት ላይ የሚፈልጓቸውን ተጫዋቾች ለመግዛት ሩጫ ውስጥ ገብተዋል።
የዝውውር…
ፌድሪኮ ኪየዛ ሊቨርፑልን ለመቀላቀል ተስማማ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 22፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ሊቨርፑል ጣሊያናዊውን የፊት መስመር አጥቂ ፌድሪኮኪየዛን ከጁቬንቲስ ለማስፈረም ተስማማ፡፡
በዝውውሩ ሊቨርፑል ለጣሊያኑ ክለብ በአጠቃላይ 13 ሚሊየን ዩሮ ይከፍላል ነው የተባለው፡፡
ዝውውሩ ሲጠናቀቅ ኪየዛ በመርሲሳይዱ ክለብ ለ4 ዓመታት የሚያቆየውን ኮንትራተት ይፈርማል የተባለ ሲሆን የህክምና ምርመራዉን ለማድረግ ዛሬ…