ስፓርት
በፕሪሚየር ሊጉ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክና አዳማ ከተማ ድል ቀናቸው
አዲስ አበባ፣ ጥር 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ12ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ዛሬ ሁለት ጨዋታዎች ተደርገዋል፡፡
ቀን 9 ሰዓት ላይ በተካሄደ ጨዋታ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባህር ዳር ከተማን 2 ለ 1 በማሸነፍ የሊጉን መሪነት አጠናክሯል፡፡
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን የማሸነፊያ ግቦች ቢንያም ጌታቸውና አዲስ ግደይ ሲያስቆጥሩ÷የባህር ዳር ከተማን ብቸኛ ግብ ደግሞ አለልኝ አዘነ አስቆጥሯል፡፡
በተመሳሳይ ምሽት 12 ሰዓት ላይ በተካሄደ ጨዋታ አዳማ ከተማ ሃዋሳ ከተማን 3 ለ 2 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡…
Read More...
ታላቁ የወንጪ ሩጫ በነገው ዕለት ይካሄዳል
አዲስ አበባ፣ ጥር 17፣ 2016 (ኤፍቢ ሲ) የኦሮሚያ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ያዘጋጀው ውድድር ነገ ማለዳ የቱሪስት መዳረሻ ስፍራ በሆነው ወንጪ ሐይቅ ዙሪያ ለመጀመሪያ ጊዜ ይካሄዳል።
የአዋቂዎች ውድድር 10 ኪሎ ሜትር እንደሚሸፍን እንዲሁም ህፃናት የሚሳተፉበት የ1 ኪሎ ሜትር ውድድር እንደተዘጋጀ የኦሮሚያ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ማቴዎስ ሰቦቃ…
የርገን ክሎፕ የ2023/24 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሲጠናቀቅ ከሊቨርፑል ይሰናበታሉ- ክለቡ
አዲስ አበባ፣ ጥር 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሊቨርፑሉ አሰልጣኝ የርገን ክሎፕ ከክለቡ የ2023/24 እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የውድድር መርሐ-ግብር ሲጠናቀቅ ከክለቡ እንደሚሰናበቱ ተሰምቷል፡፡
የተጀመረው የፕሪሚየር ሊግ ውድድር መርሐ-ግብር እስከሚጠነቀቅ ድረስ በአሰልጣኝነታቸው እንደሚቀጥሉም ተገልጿል፡፡
የመርሲሳይዱ ክልብ ሊቨርፑል አሁን ላይ የእንግሊዝ ፕሪሚየር…
የፕሪሚየር ሊጉ ጨዋታዎች በአቻ ውጤት ተጠናቀቁ
አዲስ አበባ፣ ጥር 16፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ12ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ዛሬ ሁለት ጨዋታዎች ተደርገዋል፡፡
ቀን 9 ሰዓት ላይ ኢትዮጵያ መድን እና ሻሸመኔ ከተማ ያካሄዱት ጨዋታ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቅቋል፡፡
የኢትዮጵያ መድንን ብቸኛ ግብ ወገኔ ገዛኸኝ ሲያስቆጥር÷ የሻሸመኔ ከተማን ደግሞ አብዱልቃድር ናስር አስቆጥሯል፡፡…
ሞሮኮ በአሰልጣኝ ዋሊድ ረግራጊ የሁለት ጨዋታዎች ቅጣት ይግባኝ ጠየቀች
አዲስ አበባ፣ ጥር 16፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ሞሮኮ በአሰልጣኝ ዋሊድ ረግራጊ የሁለት ጨዋታዎች ቅጣት ውሳኔ ላይ ለካፍ የይግባኝ ደብዳቤ ማስገባቷን የሀገሪቱ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስታውቋል፡፡
አሰልጣኝ ዋሊድ ረግራጊ አቻ በተጠናቀቀው የሞሮኮ እና ኮንጎ ጨዋታ በኮንጎ ብሄራዊ ቡድን አምበል ቻንሴል ምቤምባ ላይ በፈፀሙት ያልተገባ ባህሪ በካፍ የሁለት ጨዋታዎች እገዳ ተጥሎበት…
ምሽቱን የተካሄዱ የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ 5 ጨዋታዎች በአቻ ውጤት ተጠናቀቁ
አዲስ አበባ፣ ጥር 15፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኮቲዲቯር አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ጨዋታ በተመሳሳይ ሰዓት ምሽት ላይ የተካሄዱ የምድብ አምስት ሁለት ጨዋታዎች ያለምንም ጎል በአቻ ውጤት ተጠናቅቀዋል፡፡
ናሚቢያ ከማሊ እንዲሁም ደቡብ አፍሪካ ከቱኒዚያ ያደረጉት ጨዋታ ያለምንም ጎል በአቻ ውጤት ተጠናቅቋል፡፡
ይህን ተከትሎም ማሊ በ5 ነጥብ…
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና የፊታችን ማክሰኞ ይጀመራል
አዲስ አበባ፣ ጥር 15፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) 53ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና የፊታችን ጥር 21ቀን እንደሚጀመር የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አስታውቋል፡፡
መርሐ ግብሩ ከጥር 21 እስከ ጥር 26 ቀን 2016 ዓ.ም በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ለተከታታይ 6 ቀናት ነው የሚካሄደው፡፡
ውድድሩ ክልሎች፣ ከተማ አስተዳደሮች፣ ክለቦችና ተቋማት የውድድር እድል…