ስፓርት
በፍቅረኛዋ አካል ጉዳት የደረሰባት አሜሪካዊት እንስት በፓሪሱ ፓራሊምፒክ…
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 22፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በቀድሞ ፍቅረኛዋ ድብደባ ምክንያት አንድ አይኗን ያጣችውና እግሮቿ የማይታዘዙላት አሜሪካዊቷ ትሬሲ ኦቶ በፓሪሱ ፓራሊምፒክ ውድድር ሀገሯን ወክላለች፡፡
የ28 ዓመቷ ትሬሲ ኦቶ ከቢቢሲ ጋር ባደረገችው ቆይታ÷በፈረንጆቹ 2019 ከቀድሞ ፍቅረኛዋ ጋር በተለያዩ ምክንያቶች መቀጠል ባለመቻላቸው መለያየታቸውን ትናገራለ፡፡
ይህን ተከትሎም የቀድሞ ፍቅረኛዋ እሷንና ቤተሰቦቿን እገድላችኋለሁ በሚል ሲያስፈራራና ሲዝት እንደነበር ታስታውሳለች፡፡
በማስፈራራት ብቻ ያልቆመው የቀድሞ ፍቅረኛዋ ከዕለታት…
Read More...
በ5000 ሜትር የሴቶች የፍፃሜ ውድድር ኢትዮያውያን አትሌቶች አሸነፉ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 22፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ከ20 ዓመት በታች የሴቶች 5000 ሜትር የፍፃሜ ውድድር ኢትዮያውያን አትሌቶች አሸንፈዋል።
አትሌት መዲና ኢሳ በ14:39:71 አንደኛ በመውጣት የዓለም ከ20 ዓመት በታች የ5000 ሜትር ውደድርን ክብረወሰን በመስበር የወርቅ ሜዳልያ አሸንፋለች።
አትሌት መቅደስ አለምሸት ደግሞ በ14:57:44 ሁለተኛ ሆና በማጠናቀቅ የብር…
ክርስቲያኖ ሮናልዶ አልናስር የመጨረሻ ክለቡ ሊሆን እንደሚችል ፍንጭ ሰጠ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 21፣ 2016(ኤፍ ቢ ሲ) ክርስቲያኖ ሮናልዶ አሁን እየተጫወተበት ያለው የሳዑዲው አልናስር ክለብ የመጨረሻው ሊሆን እንደሚችል ከፖርቹጋል ቴሌቪዥን ጋር በነበረው ቆይታ ፍንጭ ሰጥቷል፡፡
የ39 ዓመቱ የእግር ኳስ ኮከብ ከማንቼስተር ዩናይትድ ቆይታ በኋላ በፈረንጆቹ 2023 ጥር ወር ወደ ሳዑዲ ፕሮ ሊግ ማቅናቱ ይታወሳል፡፡
የእግር ኳስ ሕይወቱን ወደ…
ማንቼስተር ዩናይትድ ማኑየል ኡጋርቴን ለማስፈረም ተስማማ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ማንቼስተር ዩናይትድ ዑራጋዊውን የአማካኝ ሥፍራ ተጫዋች ማኑየል ኡጋርቴን በ50 ሚሊየን ዩሮ ከፈረንሳዩ የእግር ኳስ ክለብ ፒኤስጂ ለማስፈረም መስማማቱ ተሰምቷል፡፡
ዛሬ የሕክምና ምርመራውን አጠናቅቆ ወደ ቀያይ ሰይጣኖቹ እንደሚቀላቀልም ተጠቅሷል፡፡
በስምምነቱ መሠረት የተጫዋቹ ውጤታማነት ታይቶ የሚጨመር 10 ሚሊየን ዩሮ…
ኢትዮጵያ የምትጠበቅባቸው ሁለት የፍጻሜ ውድድሮች ዛሬ ይካሄዳሉ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በፔሩ ሊማ የሚካሄደው 20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ከ20 ዓመት በታች ሻምፒዮና ዛሬ ሲጀመር ኢትዮጵያ የምትጠበቅባቸው ሁለት የፍጻሜ ውድድሮች ይደረጋሉ፡፡
በዚሁ መሠረት ሌሊት 7 ሰዓት ከ25 ላይ በሚካሄደው የሴቶች 5 ሺህ ሜትር ፍጻሜ አትሌት መዲና ኢሳ እና መቅደስ ዓለምእሸት ይጠበቃሉ፡፡
እንዲሁም ሌሊት 7 ሰዓት ከ55…
በቦነስ አይረስ ግማሽ ማራቶን አትሌት ገርባ ዲባባ አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአርጀንቲና ቦነስ አይረስ በተካሄደው የወንዶች ግማሽ ማራቶን ውድድር አትሌት ገርባ ዲባባ አሸነፈ፡፡
አትሌቱ 21 ኪሎ ሜትሩን 1 ሰዓት ከ26 ሴኮንድ በመግባት ማሸነፍ የቻለው፡፡
ኬኒያውያኖቹ ሙዋንጊ ኮስማስ እና ሪቻርድ ያተር ሪቻርድ 2ኛ እና 3ኛ በመሆን አጠናቀዋል፡፡
በሴቶች የግማሽ ማራቶን ደግሞ ኬኒያዊቷ ሩት…
በዳይመንድ ሊግ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸነፉ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 19፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በስዊዘርላንድ በተካሄደው በሉዛን ዳይመንድ ሊግ በ1 ሺህ 500 ሴቶች ውድድር ፣በ3ሺህ ሜትር ወንዶችና በ3ሺህ ሜትር ወንዶች መሰናክል ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸንፈዋል፡፡
አትሌት ድሪቤ ወልተጂ የ1 ሺህ 500 የሴቶች ውድድርን ቀዳሚ ሆና በመግባት ስታሸንፍ ፍሬወይኒ ሀይሉ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቅቃለች፡፡…