Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

አሰልጣኝ ፍሬው ሀይለገብርኤል ከብሔራዊ ቡድኑ ጋር ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ጥር 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን እና ከ20 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ፍሬው ኃይለገብርኤል ከብሔራዊ ቡድኑ ጋር በይፋ ተለያይተዋል። የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሆነው በ2013 ዓ.ም የተሾሙት አሰልጣኙ፤ በአራት ዓመት ቆይታቸው ቡድኑ በፈረንጆቹ 2022 እና 2024 የዓለም ዋንጫ ማጣሪያዎች እስከ መጨረሻው ዙር እንዲደርስ አስችለዋል፡፡ በተጨማሪም በ2022 በዩጋንዳ በተካሄደው የሴካፋ ከ20 ዓመት በታች ሴቶች ዋንጫ ውድድር አሸናፊ እንዲሆን…
Read More...

በግማሽ ፍጻሜ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ናይጄሪያ ከደቡብ አፍሪካ እንዲሁም ኮትዲቯር ከዴሞክራቲክ ኮንጎ ይጫወታሉ

አዲስ አበባ፣ ጥር 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በግማሽ ፍጻሜ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ናይጄሪያ ከደቡብ አፍሪካ እንዲሁም ኮትዲቯር ከዴሞክራቲክ ኮንጎ ዛሬ ምሽት ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡ ናይጄሪያ ከደቡብ አፍሪካ ለፍጻሜ ለማለፍ የሚያደርጉት ጨዋታ ምሽት 2 ሰዓት ላይ በአቢጃን ስታድ ዲ ላ ፔይክስ ይካሄዳል፡፡ ሁለቱ ቡድኖች በግማሽ ፍጻሜ በታሪክ ለ4ኛ…

በቶሩን የቤት ውስጥ ሩጫ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ጥር 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በፖላንድ ቶሩን የቤት ውስጥ ሩጫ ውድድር በተለያዩ ርቀቶች ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ አሸንፈዋል። በ1 ሺህ 500 ሜትር የሴቶች የቤት ውስጥ ሩጫ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከ1ኛ እስከ 4ኛ በመውጣት ታሪክ ሰርተዋል፡፡ በዚህም ፍሬወይኒ ሃይሉ በ1 ሺህ 500 ሜትር ሴቶች የቤት ውስጥ ሩጫ ታሪክ በርቀቱ…

ለወልቂጤ ከተማ እግርኳስ ቡድን  ከ43 ሚሊየን ብር  በላይ ተሰበሰበ

አዲስ አበባ፣ ጥር 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ተሳታፊ ለሆነው የወልቂጤ ከተማ እግርኳስ ቡድን  ከ43 ሚሊየን ብር በላይ መሰብሰቡ ተገለፀ፡፡ የወልቂጤ ከተማ እግር ኳስ ቡድን  የገቢ ማሰባሰቢያ መርኃ ግብር  በአዲስ አበባ ስካይ ላይት ሆቴል ተካሄዷል። በገቢ ማሰባሰቢያ መርኃ ገብሩ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው…

በቦስተን የኒው ባላንስ የቤት ውስጥ ውድድር ጉዳፍ ፀጋይና ለሜቻ ግርማ አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ጥር 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በቦስተን የኒው ባላንስ የዓለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ውድድር ጉዳፍ ፀጋይ እና ለሜቻ ግርማ ውድድሩን በበላይነት አጠናቅቀዋል፡፡ በ1 ሺህ 500 ሜትር የተወዳደረችው ጉዳፍ ፀጋይ ርቀቱን በ3 ደቂቃ 58 ሰከንድ ከ11 ማይክሮ ሰከንድ በሆነ ሰዓት በማጠናቀቅ ቀዳሚ ሆናለች፡፡ በዚሁ ርቀት የ18 ዓመቷ አትሌት ብርቄ ሀየሎም 3…

በኢትዮጵያ ፕሪሚየርሊግ ፋሲል ከነማና ሐዋስ ከተማ አሸንፈዋል

አዲስ አበባ፣ ጥር 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ13ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየርሊግ ፋሲል ከነማ እና ሐዋስ ከተማ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸንፈዋል፡፡ ቀን 9 ሰዓት ላይ የተካሄደው የሐዋሳ ከተማ እና ወልቂጤ ከተማ ጨዋታ በሐይቆቹ 2 ለ 1 አሸናፊነት ተጠናቋል፡፡ አሊ ሱሌማን የሐዋሳ ከተማን ሁለት ጎሎች ሲያስቆጥር አቡበከር ሳኒ የወልቂጤ ከተማን ብቸኛ ጎል አስቆጥሯል፡፡…

በእንግሊዝ ፕሪሚየርሊግ ማንቼስተር ዩናይትድ ሲያሸንፍ ቼልሲ በሜዳው ተሸንፏል

አዲስ አበባ፣ ጥር 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንቼስተር ዩናይትድ ዌስትሃም ዩናይትድን ሲያሸንፍ ቼልሲ በሜዳው በዎልቭስ ተሸንፏል፡፡ ዌስትሃምን የገጠመው ማንቼስተር ዩናይትድ 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ሲያሸንፍ ራስመስ ሆይለንድ እና አሊሃንድሮ ጋርናቾ (ሁለት) ጎሎችን አስቆጥረዋል፡፡ ተከታታይ ድሉን ማስመዝገብ የቻለው ማንቼስተር ዩናይትድ ነጥቡን…