Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

ሴኔጋል ጊኒን 2 ለ 0 ካሜሮን ደግሞ ጋምቢያን 3 ለ 2 በሆነ ውጤት አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ጥር 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ዛሬ ምሽት 2 ሰዓት ላይ በተደረጉ የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ 3 ጨዋታዎች ሴኔጋል ጊኒን 2 ለ 0 ካሜሮን ደግሞ ጋምቢያን 3ለ2 በሆነ ውጤት አሸንፈዋል፡፡ ቀድማ ማለፏን ያረጋገጠችው ሴኔጋል በ61ኛው እና በ90ኛው ደቂቃዎች በተቆጠሩ ግቦች አሸናፊ ሆናለች፡፡ ካሜሮንም በ56ኛው፣ 87ኛው እና በ91ኛው ደቂቃዎች በተገኙ ግቦች አሸናፊ መሆን ችላለች፡፡ የካሜሮንን ሁለተኛ ጎል የጋምቢያው ተጫዋች በራሱ መረብ ላይ አሳርፏል፡፡ የምድብ 4 ጨዋታዎች ከምሽቱ 5 ሰዓት ሲካሄዱ…
Read More...

አትሌት ለሜቻ ግርማ በፈረንሳይ ሌቪን በሚካሄደው የ3 ሺህ ሜትር ውድድር ይሳተፋል

አዲስ አበባ፣ ጥር 13፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም የ3 ሺህ ሜትር መሰናክል ክብረ ወሰን ባለቤት ለሜቻ ግርማ በፈረንሳይ ሌቪን በሚካሄደው የ3 ሺህ ሜትር ውድድር እንደሚሳተፍ ተገለፀ፡፡ አትሌቱ ባለፈው የውድድር ዘመን በፈረንሳይ ሌቪን በ3 ሺህ ሜትር የቤት ውስጥ ውድድር በ7 ደቂቃ 23 ሰከንድ 81 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት ሪከርድ ማሻሻሉ የሚታወስ ነው፡፡…

የጊኒ ብሔራዊ ቡድን ማሸነፉን ተከትሎ ደስታቸውን በአደባባይ ሲገልፁ የነበሩ 6 ደጋፊዎች ህይወታቸው አለፈ

አዲስ አበባ፣ ጥር 13፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአፍሪካ ዋንጫ ጊኒ ጋምቢያን ማሸነፏን ተከትሎ ደስታቸውን በአደባባይ ሲገልፁ የነበሩ ስድስት ደጋፊዎች ህይዎታቸው ማለፉ ተገለፀ፡፡ ክስተቱን ተከትሎም የሀገሪቱ እግርኳስ ፌዴሬሽን እና የቀድሞው የጊኒ ኮከብ ተጫዋች ፓስካል ፊንዶኖ ደጋፊዎች እንዲረጋጉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በአፍሪካ ዋንጫ 15 ጊዜ መሳተፍ የቻለችው ምዕራብ…

ሞሮኮ እና ዲሞክራቲክ ኮንጎ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ጥር 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ማጣሪያ ጨዋታ ሞሮኮ እና ዲሞክራቲክ ኮንጎ አንድ አቻ ተለያይተዋል፡፡ 11 ሰዓት ላይ በተካሄደው የምድብ 6 ጨዋታ ለሞሮኮ አሽራፍ ሀኪሚ እንዲሁም ለዲሞክራቲክ ኮንጎ ካቶምፓ ሙቩምፓ ጎሎቹን አስቆጥረዋል፡፡ ዲሞክራቲክ ኮንጎ ያገኘቻትን የፍፁም ቅጣት ምት አጥቂው ሴድሪች ማካምቡ ሳይጠቀምበት…

ኢትዮጵያ ከኮሎምቢያ የዓለም ዋንጫ ውጭ ሆነች

አዲስ አበባ፣ ጥር 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ የመጨረሻ ዙር ጨዋታውን ከሞሮኮ አቻው ጋር አድርጓል፡፡ ዛሬ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም የተደረገውን የመልስ ጨዋታ ኢትዮጵያ በፀሐይነሽ ጁላ ጎል ሞሮኮን 1 ለ 0 ብታሸንፍም÷ በድምር ውጤት 2 ለ 1 ተሸንፋ ከኮሎምቢያው የዓለም ዋንጫ ውጭ ሆናለች፡፡…

በታታ ሙምባይ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ቀናቸው

አዲስ አበባ፣ ጥር 12፣ 2016 ( ኤፍ ቢ ሲ) በህንድ በተካሄደ የታታ ሙምባይ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከአንድ እስከ ስምንተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀቁ፡፡ በሴቶች ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከአንድ እስከ ስምንተኛ ደረጃ በመያዝ ያጠናቀቁ ሲሆን ÷አበራሽ ምንሰዎ ፣ሙሉሃብት ፅጌ እና መድህን በጀኔ ከአንደኛ እና ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ…

በአፍሪካ ዋንጫ አንጎላ ሞሪታኒያን 3 ለ 2 አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ጥር 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አንጎላ ሞሪታኒያን 3 ለ 2 በሆነ ውጤት አሸንፋለች፡፡ ውጤቱን ተከትሎ አንጎላ ከቡርኪናፋሶ እኩል በአራት ነጥብ እና በአንድ ንጹሕ ግብ ምድቡን መምራት ችላለች፡፡ በአንጻሩ ሞሪታኒያ ያለምንም ነጥብ በምድብ አራት ግርጌ ላይ ተቀምጣለች፡፡