Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

የ2024 ፓሪስ ኦሎምፒክ ሀገር አቀፍ የችቦ ቅብብሎሽ በመቀሌ ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ጥር 19፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በፈረንጆቹ የ2024 ፓሪስ ኦሎምፒክ ሀገር አቀፍ የችቦ ቅብብሎሽ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር በመቀሌ ከተማ ተከሂዷል። በችቦ ቅብብሎሽ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብሩ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ረዳት ኮሚሽነር አትሌት ደራርቱ ቱሉ እና ሌሎች አመራሮች ተገኝተዋል። መርሐ-ግብሩ በመጪው ሐምሌ ወር 2016 ዓ.ም ለሚካሄደው 33ኛው የፓሪስ ኦሎምፒክ በማህበረሰቡ ዘንድ ከወዲሁ መነቃቃትን ለመፍጠር ያለመ መሆኑ ተገልጿል፡፡ አትሌት ደራርቱ በወቅቱ እንደተናገሩት÷ የኦሎምፒክ ችቦው ወደ ሁሉም…
Read More...

አንጎላ ናሚቢያን በማሸነፍ  ሩብ ፍጻሜው ተቀላቀለች

አዲስ አበባ፣ ጥር 18፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ አንጎላ ናሚቢያን 3 ለ 0 በማሸነፍ ወደ ሩብ ፍጻሜው ገብታለች፡፡ ምሽት 2 ሰዓት ላይ በቡዋኬ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ አዲልሰን ነቡላ፣ ጊልሰን ዳላ እና ኦገስቲኖ ሙቡሉ ለአንጎላ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል፡፡ በጨዋታው የአንጎላው ግብ ጠባቂ አዲልሰን ኔብሉ እና የናሚቢያው…

ቅዱስ ጊዮርጊስ በድሬዳዋ ከተማ 3 ለ 0 ተሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ጥር 18፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ12ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሳይጠበቅ በድሬዳዋ ከተማ 3 ለ 0 ተሸንፈዋል፡፡ ቀን 9 ሰዓት ላይ በተደረገው የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ኤፍሬም አሻሞ፣ ቻርለስ ሙሲጌ እና ሱራፌል ጌታቸው የድሬዳዋን ጎሎች አስቆጥረዋል፡፡ ውጤቱን ተከትሎም ድሬዳዋ ነጥቡን 14 በማድረስ ለጊዜው 10ኛ ደረጃ ላይ…

አትሌት ሳሙኤል ተፈራ በአስታና የ3 ሺህ ሜትር የቤት ውስጥ ሻምፒዮና አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ጥር 18፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) አትሌት ሳሙኤል ተፈራ በካዛኪስታን አስታና በተካሄደ የ3 ሺህ ሜትር የቤት ውስጥ ሻምፒዮና የአመቱን ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ አሸንፏል፡፡ አትሌቱ 7 ደቂቃ ከ33 ሴኮንድ ከ85 ማይክሮ ሴኮንድ በመግባት ነው የዓመቱን የ3 ሺህ ሜትር ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ ማሸነፉን የዓለም አትሌቲክስ መረጃ ያመላከተው፡፡ የ3 ሺህ ሜትር…

ታላቁ የወንጪ 10 ኪሎ ሜትር ሩጫ በወንጪ ደንዲ ኢኮ ቱሪዝም ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ጥር 18፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ታዋቂ አትሌቶች የተሳተፉበት ታላቁ የወንጪ 10 ኪሎ ሜትር ሩጫ በወንጪ ደንዲ ኢኮ ቱሪዝም ተካሄደ፡፡ በውድድሩ በሴቶች ጌጤ አለማየሁ፣ ፎትን ተስፋዬ እና ኑሪት አህመድ ከ1ኛ እስከ 3ኛ ያለውን ደረጃ በመያዝ በቀዳሚነት አጠናቀዋል። በወንዶች ደግሞ አትሌት አዲሱ ነጋሽ፣ ሞገስ ንኡማንና ኤሊያስ ጫኔ ተከታትለው በመግባት…

የአፍሪካ ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ዛሬ ምሽት ይካሄዳሉ

አዲስ አበባ፣ ጥር 18፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፍሪካ ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ዛሬ ምሽ ሲካሄዱ አንጎላ ከናሚቢያ እንዲሁም ናይጀሪያ ከካሜሩን ይጫዎታሉ፡፡ አንጎላ ከናሚቢያ የሚያደርጉት የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ምሽት 2 ሰዓት ላይ በቡዋኬ ሰታዴ ዴ ላ ፔይክስ ስታዲየም የሚደረግ ሲሆን በጨዋታው አንጎላ የአሸናፊነት ግምት ተሰጥቷታል፡፡ ሁለቱ ቡድኖች በታሪካቸው ካደረጉት…

በፕሪሚየር ሊጉ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክና አዳማ ከተማ ድል ቀናቸው

አዲስ አበባ፣ ጥር 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ12ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ዛሬ ሁለት ጨዋታዎች ተደርገዋል፡፡ ቀን 9 ሰዓት ላይ በተካሄደ ጨዋታ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባህር ዳር ከተማን 2 ለ 1 በማሸነፍ የሊጉን መሪነት አጠናክሯል፡፡ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን የማሸነፊያ ግቦች ቢንያም ጌታቸውና አዲስ ግደይ ሲያስቆጥሩ÷የባህር ዳር ከተማን…