Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

የሀድያ ሆሳዕና እና የአዳማ ከተማ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 2፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሀድያ ሆሳዕና እና አዳማ ከተማ 3ለ 3 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል፡፡ ጥሩ ፉክክር በታየበት በዚህ ጨዋታ አዳማ ከተማ 3 ለ 0 እየመራ ቢቆይም ሀድያ ሆሳዕና ነጥብ መጋራት ችሏል። በጨዋታው የአዳማ ከተማን ሁለት ግቦች ዳዋ ሆቴሳ ሲያስቆጥር ቀሪዋን አንድ ግብ አዲስ ተስፋዬ አስቆጥሯል፡፡ የሀድያ ሆሳዕናን ሁለት ግቦች ደግሞ ባዬ ገዛኸኝ ያስቆጠረ ሲሆን ፥ አንዷን ግብ ሠመረ ሀፍተይ ማስቆጠር ችሏል፡፡
Read More...

የስድስት ሀገራት አትሌቶችን የሚያሳትፈው የአስመራ ማራቶን የፊታችን እሑድ ይካሄዳል

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 2፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያን ጨምሮ የስድስት ሀገራት አትሌቶችን የሚያሳትፈው የአስመራ ማራቶን በመጪው እሑድ እንደሚካሄድ የኤርትራ ባህልና ስፖርት ኮሚሽን አስታውቋል፡፡ የኤርትራ ባህልና ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ዘመዴ ተክሌ ÷በውድድሩ መርሐ ግብር የወንዶች ሙሉ ማራቶን እና የ10 ኪሎ ሜትር የሴቶች ውድድርመዘጋጀቱን ገልፀዋል፡፡…

ሪያል ማድሪድ እና ቦሩሲያ ዶርትሙንድ  በቤሊንግሃም ዝውውር ሲስማሙ ሊዮኔል ሜሲ ወደ አሜሪካ ሊያቀና ነው

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 30 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ሪያል ማድሪድ እንግሊዛዊውን የቦሩሲያ ዶርትመንድ አማካይ ጁዲ ቤሊንግሃምን ለማስፈረም መስማማቱ ተሰምቷል። ሎስብላንኮዎች አማካዩን ለማስፈረም 113 ሚሊየን ፓውንድ የሚከፍሉ ሲሆን፥ ተጫዋቹም ስድስት አመታት የኮንትራት ውል እንደሚፈርም ይጠበቃል። ቤሊንግሃም ስሙ ከሊቨርፑል እና ሪያል ማድሪድ ሲያያዝ መቆየቱ ይታወሳል።…

ካሪም ቤንዜማ የሳውዲ አረቢያውን ክለብ ለመቀላቀል ተስማማ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 29፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ፈረንሳዊው የሪያል ማድሪድ አጥቂ ካሪም ቤንዜማ የሳውዲ አረቢያውን ክለብ አል ኢቲሃደን ለመቀላቀል ተስማማ፡፡ ቢቢሲ ማምሻውን ይዞት በወጣው መረጃ የባለንድኦር አሸናፊው ቤንዜማ ሪያል ማድሪድን በመልቀቅ ከአል ኢቲሃደ ጋር የ3 ዓመት ውል ፈጽሟል፡፡ የ35 ዓመቱ ቤንዜማ በሪያል ማድሪድ ቆይታው 5 የሻምፒዮንስ ሊግና 4…

የአፍሪካ ዞን 4 የጎልፍ ስፖርት ሻምፒዮና ውድድር የመክፈቻ መርሐ ግብር እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 29፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፍሪካ ዞን አራት የጎልፍ ስፖርት ሻምፒዮና ውድድር የመክፈቻ መርሐ ግብር ጦር ኃይሎች በሚገኘው ጎልፍ ክለብ እየተካሄደ ነው፡፡ በመክፈቻ መርሀ ግብሩ የባህልና ስፖርት ሚኒስትሩ ቀጄላ መርዳሳን ጨምሮ የስፖርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴዔታ አምባሳደር መስፍን ቸርነት፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንዲሁም…

የኢትዮጵያ ጠረጴዛ ቴኒስ የክለቦች ሻምፒዮና ውድድር ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 29፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) 2ኛው ዙር የኢትዮጵያ ጠረጴዛ ቴኒስ የክለቦች ሻምፒዮና ውድድር በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ መካሄድ ጀምሯል። የኢትዮጵያ ጠረጴዛ ቴኒስ ፌዴሬሽን ባዘጋጀው ውድድር ከስድስት ክለቦች የተውጣጡ ከ90 በላይ ስፖርተኞች ተሳታፊ ሆነዋል። ውድድሩ በአዋቂዎችና በታዳጊዎች በሁለቱም ፆታ የሚካሄድ ሲሆን÷በቀጣይ በቱኒዚያ ለሚካሄደው…

ዝላታን ኢብራሂሞቪች ከእግርኳስ ራሱን አገለለ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 28፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ስዊድናዊው አጥቂ ዝላታን ኢብራሂሞቪች በ41 ዓመቱ ራሱን ከእግርኳስ ዓለም ራሱን አግሏል፡፡ ግዙፉ አጥቂ በማልሞ፣ አያክስ፣ ጁቬንቱስ፣ ኢንተርሚላን፣ ኤሲሚላን፣ ባርሴሎና፣ ማንቼስተር ዩናይትድ፣ ፓሪ ሴንት ዥርሜን እና ኤል ኤ ጋላክሲ ክለቦች ተጫውቶ አሳልፏል። በእነዚህ ጊዜያት በ866 የክለብ ጨዋታዎች ላይ 511 ጎሎችን…