ስፓርት
መቻል እና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸነፉ
አዲስ አበባ፣ ጥር 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ11ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መቻል እና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸንፈዋል፡፡
9፡00 ሠዓት ላይ ድሬዳዋ ከተማን የገጠመው መቻል ከንዓን ማርክነህ እና በኃይሉ ግርማ ባስቆጠሯቸው ጎሎች 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡
እንዲሁም 12፡00 ሠዓት ላይ ኢትዮጵያ መድንን ያስተናገደው ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከመመራት ተነስቶ 4 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡
ፈቱዲን ጀማል (ሁለት)፣ አዲስ ግደይ እና ቢኒያም ጌታቸው የንግድ ባንክን ጎሎች አስቆጥረዋል፡፡
ውጤቱን ተከትሎም ኢትዮጵያ…
Read More...
ናሚቢያ ቱኒዚያን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸነፈች
አዲስ አበባ፣ ጥር 7፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ 5 ጨዋታ ናሚቢያ ቱኒዚያን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸነፈች፡፡
ናሚቢያን አሸናፊ ያደረገችውን ግብ ሆቶ በ88ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል፡፡
በዚሁ ምድብ የሚገኙት ማሊና ደቡብ አፍሪካ ምሽት 5 ሰዓት ላይ የሚጫወቱ ይሆናል፡፡
ቀደም ብሎ በተደረገ የምድብ 4 ጨዋታ ቡርኪናፋሶ…
ቡርኪናፋሶ በተጨማሪ ሰዓት ባስቆጠረችው ግብ ሞሪታኒያን አሸነፈች
አዲስ አበባ፣ ጥር 7፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በምድብ 4 የማጣሪያ ጨዋታ ቡርኪናፋሶ በተጨማሪ ሰዓት ባስቆጠረችው ግብ ሞሪታኒያን 1 ለ 0 አሸነፈች።
ለቡርኪናፋሶ የማሸነፊያ ግብን በርትራንድ ትራኦሬ በ96ኛው ደቂቃ ላይ ማስቆጠር ችሏል፡፡
በአፍሪካ ዋንጫ በምድብ 5 ጨዋታዎች ምሽት 2 ሰዓት ላይ ቱኒዝያ ከናሚቢያ እንዲሁም ከምሽቱ 5 ሰዓት ላይ…
ጆዜ ሞሪንሆ ከሮማ አሰልጣኝነታቸው ተባረሩ
አዲስ አበባ፣ ጥር 7፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ጆዜ ሞሪንሆ ከሮማ አሰልጣኝነታቸው መባረራቸው ተሰምቷል፡፡
ለስንብታቸው የቡድኑ ውጤት ማጣት እና ከዳኞች ጋር የሚፈጥሩት አለመግባባት ምክንያት መሆናቸው ተገልጿል፡፡
ሮማ በሴሪአው ካደረጋቸው የመጨረሻዎቹ ስድስት ጨዋታዎች አንዱን ብቻ ማሸነፍ የቻለ ሲሆን በኮፓ ኢታሊያም በላዚዮ መሸነፉ…
በአፍሪካ ዋንጫ ካሜሮን እና ጊኒ በአቻ ውጤት ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ጥር 6፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ካሜሮን እና ጊኒ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል።
የካሜሮንን ብቸኛ ግብ ማሪ ማግሪን ሲያስቆጥር ÷ የጊኒን ደግሞ ሞሃመድ ባዮ አስቀጥሯል፡፡
የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ማጣሪያ ጨዋታ መርሐ- ግብር ሲቀጥል ምሽት 5 ሰዓት አልጀሪያ ከአንጎላ ይጫወታሉ፡፡
በፕሪሚየር ሊጉ ሲዳማ ቡና ባሕር ዳር ከተማን 2 ለ 0 አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ጥር 6፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ11ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሲዳማ ቡና ባሕር ዳር ከተማን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ወሳኝ ሶስት ነጥብ አሳክቷል፡፡
ቀን 12 ሰዓት ላይ በተካሄደው ጨዋታ የሲዳማ ቡናን ግቦች ጊት ጋትኩት እና ፍቅረየሱስ ተክለብርሃን አስቆጥረዋል፡፡
በጨዋታው የባሕርዳር ከተማው ተከላካይ ያሬድ ባዬ በፈጸመው ጥፋት በቀይ…
በአፍሪካ ዋንጫ ሴኔጋል ጋምቢያን 3 ለ 0 አሸነፈች
አዲስ አበባ፣ ጥር 6፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ማጣሪያ ጨዋታ ሴኔጋል ጋምቢያን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፋለች፡፡
የሴኔጋልን የማሸነፊያ ግቦች ፔፔ ጉዮ እና ላሚን ካማራ አስቆጥረዋል፡፡
በጨዋታው የጋምቢያው ተከላካይ ኢብራሂማ አዳምስ በፈፀመው ያልተገባ ባህሪ በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል፡፡
የአፍሪካ ዋንጫ መርሐ ግብር ምሽት…