ስፓርት
ማንቼስተር ዩናይትድ እና ስፖርቲንግ ሊዝበን በብሩኖ ፈርናንዴዝ ዝውውር ተስማምተዋል
አዲስ አበባ ፣ ጥር 20 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የጥር ወር የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ሊዘጋ ሁለት ቀናት ቀርተውታል።
ክለቦችም ራሳቸውን ለማጠናከር በዝውውር መስኮቱ እየተሳተፉ ይገኛል።
ለረጅም ጊዜያት የፖርቹጋላዊው አማካይ ብሩኖ ፈርናንዴዝ ፈላጊ ሆኖ የቆየው የእንግሊዙ ማንቼስተር ዩናይትድ ፍላጎቱን ለማሳካት ተቃርቧል።
የላንክሻየሩ ክለብ ከፖርቹጋሉ ስፖርቲንግ ሊዝበን ጋር በተጫዋቹ የዝውውር ዋጋ ስምምነት ላይ መድረሱ እየተነገረ ነው።
ክለቡ ለተጫዋቹ የተጠየቀውን እስከ 68 ሚሊየን ፓውንድ የሚደርስ የዝውውር ሂሳብ ለመክፈል…
Read More...
ኢትዮጵያ በአፍሪካ የልዩ ኦሊምፒክ ውድድር 3 ሜዳሊያዎችን አገኘች
አዲስ አበባ፣ ጥር 20፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በግብፅ ካይሮ እየተካሄደ ባለው የአፍሪካ ልዩ ኦሊምፒክ ውድድር ኢትዮጵያ 3 ሜዳሊያዎች አገኘች።
የአእምሮ እድገት ውስንነት ያለባቸው ስፖርተኞች የሚሳተፉበት የአፍሪካ የልዩ ኦሊምፒክ ውድድር በካይሮ በአትሌቲክስ፣ በእግር ኳስ፣ በቅርጫት ኳስ እና በቦሽያ ስፖርት እየተካሄደ ይገኛል።
ኢትዮጵያ በአትሌቲክስ ስፖርት በአራት…
ለቶኪዮ 2020 ኦሎምፒክ ዝግጅትና ተሳትፎ 1 ቢሊየን ብር የመሰብሰብ ግብ ተቀምጧል
አዲስ አበባ፣ ጥር 19፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ለቶኪዮ ኦሎምፒክ ዝግጅትና ተሳትፎ አንድ ቢሊዮን ብር የመሰብሰብ ግብ መቀመጡን የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ገለጸ።
ኮሚቴው ዛሬ የቶኪዮ 2020 ኦሎፒክ ዝግጅትን በተመለከተ የሚጠበቁ ተግባራትን አስመልክቶ ውይይት አካሂዷል።
በዚሁ መሰረት ኮሚቴው የሚያከናውናቸው ዋና ዋና ተግባራት ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
በውይይቱ…
የከተማ አስተዳደሩ ለኢትዮጵያ ቡና እና ቅዱስ ጊዮርጊስ የስታዲየም መገንቢያ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ሰጠ
አዲስ አበባ፣ ጥር 19፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለኢትዮጵያ ቡና እና ቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ክለቦች የስታዲየም መገንቢያ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ሰጠ።
የስታዲየም እና የስፖርት ማዕከል መገንቢያ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታውን ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ ለኢትዮጵያ ቡና እና ቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ክለቦች ማስረከባቸውን የከተማ…
አንጋፋው የቅርጫት ኳስ ተጫዋች ኮቢ ብሪያንትና የ13 ዓመት ልጁ በሄሊኮፕተር አደጋ ህይወታቸው አለፈ
አዲስ አበባ፣ ጥር 18 ፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) አሜሪካዊው የቅርጫት ኳስ ተጫዋች ኮቢ ብሪያንት ከልጁ ጂያና ጋር በሄሊኮፕተር አደጋ ህይወቱ አለፈ።
ካሊፎርኒያ ካላባሳስ ከተማ በተከሰተው የሄሊኮፕተር አደጋ ኮቢ ብሪያንት እና ልጁን ጨምሮ የዘጠኝ ሰዎች ህይወት ማለፉ ተነግሯል።
የ41 ዓመቱ ኮቢ ብሪያንት በግል ሄሊኮፕተር እየተጓዘ በነበረበት ወቅት ሄሊኮፕተሩ ተከስክሶ…
ዩጋንዳ የኢትዮጵያ የሴቶች ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድንን በማሸነፍ ወደ ቀጣዩ ዙር አለፈ
አዲስ አበባ፣ ጥር 17 ፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ የሴቶች ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በህንድ አስተናጋጅነት ለሚካሄደው የዓለም የሴቶች ከ17 ዓመት በታች የዋንጫ ውድድር ለማለፍ ሲያደርግ ከነበረው ቅድመ ማጣሪያ ውጪ ሆነ፡፡
ብሄራዊ ቡድኑ በዛሬው ዕለት በባህርዳር ዓለም አቀፍ ስታድየም የዩጋንዳ አቻውን አስተናግዶ 3 ለ 1 ተሸንፎ ነው ከቅድመ ማጣሪያ ውጪ…
በፕሪምየር ሊጉ አራት ጨዋታዎች በመሸናነፍ ተጠናቀቁ
አዲስ አበባ፣ ጥር 17 ፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በዛሬው ዕለት የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ 10ኛ ሳምንት ጨዋታዎች በአዲስ አበበ እና በክልል ከተማዎች ተካሂደዋል፡፡
ፋሲለደስ ስታድየም ላይ ሲዳማ ቡናን ያስተናገደው ፋሲል ከነማ 1 ለ 0 በማሸነፍ በ18 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃ መቀመጥ ችሏል፡፡
አዳማ ከተማ ሀድያ ሆሳዕናን አስተናግዶ 2 ለ 0 ያሸነፈ ሲሆን በዚህም በሁለት…