ስፓርት
ኢትዮጵያ የምትጠበቅበት የሴቶች 10 ሺህ ሜትር ፍጻሜ ዛሬ ምሽት ይካሄዳል
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 3፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ33ኛው የፓሪስ ኦሊምፒክ ኢትዮጵያ የምትጠበቅበት የሴቶች 10 ሺህ ሜትር ፍጻሜ ውድድር ዛሬ ምሽት ይካሄዳል፡፡
በፍጻሜው አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ፣ አትሌት ጽጌ ገብረሰላማና አትሌት ፎትዬን ተስፋይ ኢትዮጵያን በመወከል ብርቱ ፉክክር ያደርጋሉ፡፡
ውድድሩ ምሽት 3 ሰዓት ከ57 ደቂቃ ላይ በስታደ ደ ፍራንስ ብሔራዊ ስታዲየም የሚካሄድ ይሆናል፡፡
በፓሪስ ኦሊምፒክ ኢትዮጵያ እስካሁን በሴቶች 800 ሜትርና በወንዶች 10 ሺህ ሜትር 2 የብር ሜዳሊያ ብቻ በማግኘት በደረጃ ሰንጠረዡ 63ኛ ላይ…
Read More...
በ1500 ሜትር ማጣሪያ ጉዳፍ ፀጋይና ድርቤ ወልተጂ ለፍጻሜ አለፉ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 2፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ1500 ሜትር የሴቶች ግማሽ ፍጻሜ ውድድር አትሌት ጉዳፍ ጸጋይና ድርቤ ወልተጂ አልፈዋል፡፡
በፓሪስ እየተካሄደ በሚገኘው 33ኛው የኦሊምፒክ ጨዋታዎች የዛሬ መርሐ-ግብር የ1 ሺህ 500 ሜትር ሴቶች የግማሽ ፍጻሜ ውድድር ምሽት ላይ ተካሂዷል፡፡
አትሌት ድርቤ ወልተጂ 1ኛ ደረጃ እንዲሁም አትሌት ጉዳፍ ጸጋይ 4ኛ ደረጃ…
አትሌት ለሜቻ ግርማ በመልካም የጤና ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ተገለፀ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 2፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የ3 ሺህ መስናክል አትሌት ለሜቻ ግርማ ካጋጠመው ጉዳት አገግሞ በመልካም የጤና ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ተገለፀ፡፡
አትሌቱ ትናንት ምሽት በፈረንሳይ ፓሪስ ኦሊምፒክ በተካሄደው የወንዶች 3 ሺህ ሜትር መሰናክል ውድድር በመጨረሻ ዙር የመሰናከሉ ጠልፎት በመውደቁ ጉዳት ማስተናገዱ ይታወሳል፡፡
በዚህም ወደ ሆስፒታል ገብቶ…
እሁድ ሊካሄድ የነበረው የአሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫ ጨዋታ ተራዘመ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የፊታችን እሁድ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮጵያ ቡና መካከል ሊደረግ የነበረው የአሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫ ጨዋታ ተራዘመ፡፡
ጨዋታው በአዲስ አበባ ስታዲየም ሐምሌ 5 ቀን 2016 ዓ.ም ሊከናወን ታስቦ የነበረ ቢሆንም ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በማኅበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል፡፡…
‘አሰልጣኟ አይደለህም፣ አናውቅህም’ ተብየ ኦሊምፒኩን እንዳልከታተል ተደርጌያለሁ – የአትሌት ጽጌ ዱጉማ አሰልጣኝ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ‘አሰልጣኟ አይደለህም፣ አናውቅህም’ ተብየ ኦሊምፒኩን እንዳልከታተል ተደርጌያለሁ ሲል የአትሌት ጽጌ ዱጉማ አሰልጣኝ ዓለሙ ዋቅጅራ ተናገረ፡፡
አሰልኙ የፓሪስ ኦሊምፒክ መለያ ባጅ መከልከሉን ተክትሎ በኢትይጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ አመራሮች ላይ ቅሬታውን አቅርቧል፡፡
ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ቆይታ ያደረገው አሰልጣኝ…
በ5 ሺህ ሜትር የወንዶች ሩጫ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ለፍጻሜ ደረሱ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ33ኛው የፓሪስ ኦሊምፒክ በ5 ሺህ ሜትር የወንዶች ሩጫ አትሌት ሐጎስ ገብረ ሕይወት፣ ቢንያም መሐሪ እና አዲሱ ይሁኔ ለፍጻሜ አልፈዋል፡፡
የ5 ሺህ ሜትር የወንዶች ማጣሪያ ውድድር 6 ሰዓት ከ10 ላይ ተካሂዷል፡፡
በዚህም አትሌት ሐጎስ በምድብ አንድ 2ኛ እንዲሁም በምድብ ሁለት ቢንያም መሐሪና አዲሱ ይሁኔ በቅደም ተከተል…
ኢትዮጵያ የምትሳተፍበት የ3 ሺህ ሜትር የወንዶች መሰናክል ፍጻሜ ዛሬ ይካሄዳል
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ33ኛው የፓሪስ ኦሊምፒክ የዛሬ መርሐ-ግብሮች ኢትዮጵያ የምትሳተፍባቸው የፍጻሜ እና የማጣሪያ ውድድሮች ይካሄዳሉ፡፡
በዚሁ መሠረት ምሽት 4 ሠዓት ከ43 ላይ በሚካሄደው 3 ሺህ ሜትር የወንዶች የፍጻሜ ውድድር÷ አትሌት ለሜቻ ግርማ፣ ሳሙኤል ፍሬው እና ጌትነት ዋለ ይሳተፋሉ፡፡
እንዲሁም ቀን 6 ሠዓት ከ10 ላይ በሚካሄደው…