Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

የፕሪሚየር ሊጉ የዕጣ ማውጣት ሥነ-ሥርዓት የፊታችን ረቡዕ ይከናወናል

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ2017 የጨዋታ መርሐ-ግብር የዕጣ ማውጣት ሥነ-ሥርዓት ረቡዕ ነሐሴ 15 ቀን 2016 ዓ.ም እንደሚካሄድ ተገለጸ፡፡ የዕጣ ማውጣት ሥነ-ሥርዓቱ የሚካሄደው በኢትዮጵያ ፕሪማየር ሊግ አክሲዮን ማኅበር ጽሕፈት ቤት መሆኑም ተገልጿል፡፡ 19 ክለቦች የሚሳተፉበት የ2017 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ መስከረም 10 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚጀምር ይታወቃል።
Read More...

ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በሰጡኝ እውቅና እና ምስጋና ተደስቻለሁ – አትሌት ታምራት ቶላ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በሰጡኝ እውቅና እና ምስጋና ተደስቻለሁ ሲል በፓሪስ ኦሊምፒክ ለኢትዮጵያ ብቸኛውን የወርቅ ሜዳሊያ ያስገኘው አትሌት ታምራት ቶላ ገለጸ፡፡ በፓሪስ ኦሊምፒክ ለተሳተፈው የኢትዮጵያ ልዑክ የእውቅናና ሽልማት መርሐ ግብር በተካሄደበት ወቅት አትሌት ታምራት÷ ጉዳት ላይ በመሆኑ በማራቶን የመወዳደር እድሉን…

በፓሪስ ኦሊምፒክ ለተሳተፈው የኢትዮጵያ ልዑክ በብሔራዊ ቤተ መንግስት የእውቅናና የሽልማት መርሐ ግብር ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 7፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ)በፓሪስ በተካሄደው 33ኛው የኦሊምፒክ ጨዋታዎች ለተሳተፈው የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በብሔራዊ ቤተ መንግስት የእውቅናና የሽልማት መርሐ ግብር ተካሂዷል፡፡ በመርሃ ግብሩ ፕሬዚዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችና የስፖርቱ ቤተሰቦች ተገኝተዋል፡፡ በእውቅናና የሽልማት መርሃ…

 ኢትዮጵያ ከ12 ዓመት በኋላ በአትሌት አበባ አረጋዊ የነሐስ ሜዳሊያ አገኘች

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 7፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በፈረንጆቹ 2012 በለንደን በተካሄደው የአሊምፒክ ጨዋታዎች ኢትዮጵያን በ1 ሺህ 500 ሜትር የወከለችው አትሌት አበባ አረጋዊ ከ12 ዓመት በኋላ ሜዳሊያዋን አግኝታለች። አትሌቷ ከ12 ዓመት በፊት በለንደን በተካሄደው የ1 ሺህ 500 ሜትር የሴቶች ፍፃሜ ውድድር 5ኛ በመውጣት አጠናቃለች፡፡ ይሁን እንጂ በውጤቱ ተሳትፎ…

ከኢትዮጵያ ርቆ የቆየውን የማራቶን ኦሊምፒክ ድል በማስመለሴ ደስ ብሎኛል – አትሌት ታምራት ቶላ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 7፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ከኢትዮጵያ ርቆ የቆየውን የማራቶን ኦሊምፒክ ድል በማስመለሴ ደስ ብሎኛል ሲል በኦሊፒኩ በወንዶች ማራቶን የወርቅ ሜዳሊያ አሸናፊው ታምራት ቶላ ተናገረ፡፡ አትሌት ታምራት ቶላን ጨምሮ በፈረንሳይ ፓሪስ በተካሄደው 33ኛው የኦሊምፒክ ጨዋታዎች የተሳተፈው የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን ዛሬ ማለዳ አዲስ አበባ ሲደርስ ደማቅ አቀባበል…

31 ክብረ ወሰኖች የተሻሻሉበት የፓሪሱ ኦሊምፒክ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 6፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በፈረንሳይ አስተናጋጅነት የተካሄደው 33ኛው የፓሪሱ ኦሊምፒክ 31 አዳዲስ ክብረ ወሰኖች ሲመዘገቡበት በርካታ አይረሴ ድራማዊ ክስተቶችንም አስተናግዶ አልፏል፡፡ የደቡብ ኮሪያ አትሌቶች በመድረኩ የሰሜን ኮሪያ ተብለው መጠራታቸው እንዲሁም በደቡብ ሱዳን ብሄራዊ መዝሙር ምትክ የሱዳን ብሄራዊ መዝሙር መለቀቁ ኦሎምፒኩን አነጋጋሪ…

የፓሪስ ኦሊምፒክ የመዝጊያ ሥነ- ሥርዓት ዛሬ ምሽት ይካሄዳል

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 5፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የ33ኛው የኦሊምፒክ ጨዋታዎች የመዝጊያ ሥነ-ሥርዓት 80 ሺህ ተመልካቾችን በሚያስተናግደው በስታድ ደ ፍራንስ ብሔራዊ ስታዲየም ከምሽቱ 4 ሠዓት ጀምሮ ይከናወናል፡፡ የኦሊምፒክ ባንዲራም 34ኛውን የኦሊምፒክ ጨዋታዎች በፈረንጆቹ 2028 ለምታስተናግደው ሎስ አንጀለስ የውድድር አዘጋጆች የማስተላለፍ መርሐ-ግብር ይከናወናል፡፡…