ስፓርት
ሐጎስ ገብረህይወት በ5 ሺህ ሜትር የሩጫ ውድድር አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 22፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያዊው አትሌት ሐጎስ ገብረህይወት በዳይመንድ ሊግ የ5 ሺህ ሜትር የወንዶች ሩጫ ውድድር አሸንፏል፡፡
በውድድሩ 12፡36፡73 ሰዓት በመግባት ሲያሸንፍ ፥ በ5ሺህ ሜትር ሩጫ ውድድር ሪከርድ ለመስበር በሁለት ሰከንድ ዘግይቶ መግባቱ ተገልጿል፡፡
አትሌቱ በተሳተፈበት በዚህ ውድድርም በታሪክ የምንጊዜም ሁለተኛውን ፈጣን ሰዓት ማስመዝገቡን ከዓለም አትሌቲክስ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
Read More...
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አዲስ የትጥቅ ብራንድ ይፋ አደረገ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ቱርክ ከሚገኝ የትጥቅ አምራች ድርጅት ጋር በመተባበር “ሀገሬ” የተሰኘ የራሱን ብራንድ ማስተዋወቁን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታወቀ፡፡
የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ ጂራ እንደገለጹት÷ ፌዴሬሽኑ ከተቋሙ ጋር ያደረገው የመግዛት እና የመሸጥ ስምምነት የጊዜ ገደብ የለውም፡፡
ፌዴሬሽኑ ያስተዋወቀው የትጥቅ ብራንድ…
ቪንሴንት ኮምፓኒ የባየር ሙኒክ አሰልጣኝ ሆነ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የጀርመኑ ክለብ ባየር ሙኒክ ቤልጂየማዊውን ቪንሴንት ኮምፓኒን በአሰልጣኝነት መሾሙን አስታውቋል፡፡
ኮምፓኒ ባየር ሙኒክን በኃላፊነት የተረከበው የቀድሞው የቡድኑ አሰልጣኝ ቶማስ ቱሄል መሰናበቱን ተከትሎ ነው፡፡
በዚህም አሰልጣኝ ቪንሴንት ኮምፓኒ ባየር ሙኒክን ለሦስት የውድድር ዓመታት ለማሰልጠን እስከ 2027 የሚያቆየውን…
አትሌት ሱቱሜ አሰፋ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ቡድንን ተቀላቀለች
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) አትሌት ሱቱሜ አሰፋ በ2024ቱ የፓሪስ ኦሊምፒክ ኢትዮጵያን በመወከል የሚሳተፈው የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ቡድን ስብስብ ውስጥ ተካተች፡፡
አትሌቷ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ግንቦት 8 በፓሪስ ኦሊምፒክ ኢትዮጵያን በማራቶን የሚወክሉ አትሌቶችን ስም ዝርዝር ይፋ ሲያደርግ ሳትካተት መቅረቷ ይታወሳል።
ይህንን ተከትሎ አትሌቷ…
በኦታዋ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታዎች አሸነፉ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 18፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦታዋ በተካሄደው የማራቶን ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታዎች ድል ቀንቷቸዋል፡፡
በወንዶች ማራቶን ሌንጮ ተስፋዬ ርቀቱን 2 ሰዓት 12 ደቂቃ ከ41 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በማጠናቀቅ ቀዳሚ ሆኗል፡፡
ሌላኛው አትሌት አዳሙ ጌታሁን ደግሞ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቅቋል፡፡
በተመሳሳይ በሴቶች…
በፕሪሚየር ሊጉ ኢትዮጵያ ቡና ሃምበሪቾን 6 ለ 1 አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 18፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ26ኛው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ኢትዮጵያ ቡና ሃምበሪቾን 6 ለ 1 በሆነ ሰፊ ልዩነት አሸንፏል።
የኢትዮጵያ ቡናን ግቦች መሐመድ ኑር ናስር (2)፣ አማኑኤል ዮሐንስ (ፍ)፣ አማኑኤል አድማሱ፣ ጫላ ተሺታና የሃምበሪቾ ግብ ጠባቂ ምንታምር መለሰ (በራሱ ግብ ላይ) አስቆጥረዋል፡፡
የሃምበሪቾን ብቸኛ ግብ ደግሞ…
በዩጂን ዳይመንድ ሊግ ድርቤ ወልተጂ እና ጽጌ ገብረሰላማ በተለያዩ እርቀቶች አሸነፉ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 18፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በዩጂን ዳይመንድ ሊግ ድርቤ ወልተጂ በ 1 ሺህ 500 እና ጽጌ ገብረሰላማ በ5 ሺህ ሜትር ቀዳሚ በመሆን አሸነፉ።
በ1 ሺህ 500 ሜትር ሴቶች አትሌት ድርቤ ወልተጂ 3 ደቂቃ 53 ሴኮንድ ከ75 ማይክሮ ሴኮንድ በመግባት በቀዳሚነት አጠናቃለች፡፡
በሌላ ርቀት የኢትዮጵያውያን አትሌቶች የበላይነት ጎልቶ በታየበት 5 ሺህ…