ስፓርት
ፋሲል ከነማ ኢትዮጵያ መድንን 2 ለ 0 አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 30፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ17ኛ ሣምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ፋሲል ከነማ ኢትዮጵያ መድንን 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡
10፡00 ሠዓት ላይ በድሬዳዋ ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የፋሲል ከነማን የድል ጎሎች ጌታነህ ከበደ በፍፁም ቅጣት ምት እና ናትናኤል ማስረሻ በጨዋታ አስቆጥረዋል፡፡
ውጤቱን ተክትሎም አፄዎቹ ነጥባቸውን ወደ 29 ከፍ በማድረግ 4ኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጡ÷ ኢትዮጵያ መድን በነበረበት 13ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡
ምሽት 1፡00 ሠዓት ላይ በተካሄደው ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ በዳዊት ተፈራ (2)…
Read More...
ማንቼስተር ዩናይትድ ኤቨርተንን 2 ለ 0 አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 30፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ28ኛ ሣምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንቼስተር ዩናይትድ ኤቨርተንን 2 ለ 0 አሸነፈ፡፡
የዩናይትድን የማሸነፊያ ጎሎች ማርከስ ራሽፎርድ እና ቡሩኖ ፈርናንዴዝ በፍፁም ቅጣት ምት አስቆጥረዋል፡፡
ሁለቱም የፍፁም ቅጣት ምቶች በአርጀንቲናዊው የመስመር አጥቂ ጋርናቾ የተገኙ ሲሆን÷ በውድድር ዓመቱም ለክለቡ ሁለት ፍፁም…
13ኛው የመላ አፍሪካ ጨዋታ ተከፈተ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 30፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) እስከ መጋቢት 13 ቀን 2016 ዓ.ም የሚቆየው 13ኛው የመላ አፍሪካ ጨዋታ በጋና አክራ በይፋ ተከፍቷል፡፡
በመክፈቻ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ÷ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ መሃማት፣ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽነሮች፣ የጋና ፕሬዚዳንት ናና አኩፋ ዶን ጨምሮ ተጋባዥ እንግዶችና ታዋቂ ግለሰቦች ተገኝተዋል፡፡
ውድድሩን…
የሜሲን ስም በመጥራት ከሃማስ እገታ የተረፉት የ90 ዓመት አዛውንት
አዲስ አበባ፣ የካቲት 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የ90 ዓመቷ አዛውንት የሊዮኔል ሜሲን ስም በመጥራት ከሃማስ እገታ መትረፋቸው መሰማቱ አነጋጋሪ ሆኗል።
ሃማስ በእስራኤል ላይ ጥቃት በፈፀመበት በፈረንጆቹ ጥቅምት 7 ቀን 2023 ዕለት ነገሩ የተፈጸመው።
በዕድሜ የገፉት የ90 ዓመቷ አዛውንት ኤስተር ኩኒዮ ቤታቸው ውስጥ ከተቀመጡበት የሃማስ አጋቾች በድንገት ይገቡና…
አትሌት ቀነኒሳ በቀለ እና ትዕግስት አሰፋ በለንደን ማራቶን ይሳተፋሉ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) አትሌት ቀነኒሳ በቀለ እና የወቅቱ የሴቶች ማራቶን ክበረ ወሰን ባለቤት ትዕግስት አሰፋ በ2024 የለንደን ማራቶን ውድድር እንደሚሳተፉ የለንደን ማራቶን አዘጋጅ ኮሚቴ አስታውቋል፡፡
የ41 ዓመቱ አትሌት ቀነኒሳ በ2023ቱ የቫሌንሲያ ማራቶን 2 ሰዓት ከ4 ደቂቃ ከ9 ሰከንድ በመግባት በአንጋፋ ዕድሜ ዘርፍ አዲስ ክብረወሰን…
በአፍሪካ ቀዳሚ ሆኖ ያጠናቀቀው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑክ አዲስ አበባ ገባ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በስኮትላንድ ግላስኮው በተካሄደው 19ኛው የዓለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና በአፍሪካ ቀዳሚ ሆኖ ያጠናቀቀው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑክ አዲስ አበባ ገባ።
የባህልና የስፖርት ሚኒስትር ዴዔታ አምባሳደር መስፍን ቸርነት እና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ…
በግላስጎ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ ከአፍሪካ አንደኛ በመሆን አጠናቀቀች
አዲስ አበባ፣ የካቲት 25፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ19ኛው የዓለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ ከአፍሪካ አንደኛ ከዓለም ደግሞ አምስተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቅቃለች።
19ኛው የዓለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና በፈረንጆቹ ከመጋቢት 1 እስከ 3 ቀን በስኮትላንዷ መዲና ግላስጎ ሲካሄድ የቆየ ሲሆን÷ በሻምፒዮናው ከ130 በላይ ሀገራት የተወጣጡ ከ650 በላይ…