Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

በአፍሪካ ዋንጫ ናይጄሪያ እና ኢኳቶሪያል ጊኒ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ጥር 5፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአፍሪካ ዋንጫ የሁለተኛ ቀን ውሎ የተገናኙት ናይጄሪያ እና ኢኳሪያል ጊኒ 1 አቻ በሆነ ውጤት ተለያይተዋል፡፡ ቪክቶር ኦሲሜን ለናይጄሪያ እንዲሁም ጆሴፍ ማሽን ለኢኳሪያል ጊኒ ጎሎች አስቆጥረዋል፡፡ የአፍሪካ ዋንጫ መርሐ- ግብሮች ምሽት መካሄዳቸውን ሲቀጥሉ 2፡00 ሰዓት ላይ ግብጽ ከሞዛምቢክ ይገናኛሉ፡፡ በተመሳሳይ በዛሬው የጨዋታ-መርሐ ግብር ምሽት 5፡00 ሰዓት ላይ ጋና ከኬፕ ቨርዴ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
Read More...

የጃንሜዳ ኢንተርናሽናል ሀገር አቋራጭ ውድድር ተጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ ጥር 5፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) 41ኛው የጃንሜዳ ኢንተርናሽናል ሀገር አቋራጭ ውድድር መጠናቀቁን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አስታውቋል፡፡ በ6 ኪሎ ሜትር የወጣት ሴቶች ሩጫ አትሌት የኔዋ ንብረት ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ስታሸንፍ አሳየች አድነው በተመሳሳይ ከንግድ ባንክ 2ኛ እንዲሁም ሽቶ ጉሚ ከኦሮሚያ ኮንስትራክሽን ኢንጅነሪንግ 3ኛ ደረጃን ይዘዋል፡፡…

በ34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የመክፈቻ ጨዋታ አስተናጋጇ ኮትዲቯር አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ጥር 4፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የመክፈቻ ጨዋታ አስተናጋጇ ኮትዲቯር ጊኒ ቢሳውን 2 ለ 0 በማሸነፍ ሶስት ነጥብ አግኝታለች። ለኮትዲቯር የማሸነፊያ ግቦቹን ገና ጨዋታው በተጀመረ አራተኛ ደቂቃ ላይ ፎፋና ሲያስቆጥር፥ ሁለተኛዋን ግብ ደግሞ ክራሶ ከእረፍት በኋላ 58ኛ ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል። #Ethiopia ወቅታዊ፣ትኩስ እና…

በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ቼልሲ ድል ቀናው

አዲስ አበባ፣ ጥር 4፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ21ኛ ሳምንት ጨዋታውን በሜዳው ያደረገው ቼልሲ ድል ቀናው። ፉልሃምን ያስተናገደው ቼልሲ ከእረፍት በፊት ፓልመር በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠረው ግብ 1 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ሶስት ነጥብ ይዞ ወጥቷል። በዚህም ነጥቡን 31 በማድረስ በፕሪሚየር ሊጉ ስምንተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ሊጉን…

በፕሪሚየር ሊጉ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ተጋጣሚያቸውን ረቱ

አዲስ አበባ፣ ጥር 3፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ10ኛ ሣምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ፋሲል ከነማ ወልቂጤ ከተማን እንዲሁም ወላይታ ድቻ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን አሸንፈዋል፡፡ 9፡00 ሠዓት ላይ በአዳማ ሣይንስና ቴክኖሎጂ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ጌታነህ ከበደ ከመረብ ባገናኛት ብቸኛ ጎል ፋሲል ከነማ ወልቂጤ ከተማን አሸንፏል፡፡ ዐፄዎቹ 1 ለ0 ማሸነፋቸውን ተከትሎም…

የ2023 አፍሪካ ዋንጫ አዘጋጇ ኮትዲቯር

አዲስ አበባ፣ ጥር 3፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የ2023 አፍሪካ ዋንጫ አዘጋጇ ምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ኮትዲቯር ዝግጅቷን አጠናቃ እንግዶቿን እየተቀበለች ነው። የውድድሩ ተሳታፊ ሀገሮች ኮትዲቯር ገብተው የውድድሩን መጀመር በመጠባበቅ ላይ ናቸው። የዘንድሮሮውን አህጉራዊ ውድድር ያዘጋጀችው ኮትዲቯር በፈረንጆቹ መስከረም 2002 የተከሰተው ወታደራዊ አመፅ ብዙ ሰብዓዊ እና…

ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ናኦሚ ግርማ የአሜሪካ የ2023 የምርጥ ተጫዋች ሽልማትን አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ጥር 3፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ለሳን ዲያጎ ዌቭ የሴቶች ቡድን እየተጫወተች የምትገኘው ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ናኦሚ ግርማ የአሜሪካ የ2023 የሴቶች ምርጥ ተጫዋች ሽልማትን አሸንፋለች፡፡ በዚህም የ23 አመቷ ናኦሚ በአሜሪካ ሴቶች እግርኳስ ታሪክ የመጀመሪያዋ ተከላካይ እና ሁለተኛዋ ጥቁር የአመቱ ምርጥ ሴት ተጫዋች ሽልማት አሸናፊ መሆን ችላለች፡፡ ናኦሚ…