Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

ሉሲዎቹ የአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ ማጣሪያ ጨዋታቸውን ዛሬ ያደርጋሉ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ ማጣሪያ ጨዋታውን ቀን 9 ሰዓት ከብሩንዲ አቻው ጋር በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ያካሂዳል ። በአሰልጣኝ ፍሬው ኃይለገብርኤል የሚሰለጥነው ብሔራዊ ቡድኑ÷ 26 ተጫዋቾችን በመያዝ ዝግጅቱን ከጳጉሜን 3 ቀን ጀምሮ በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ሲያደርግ ቆይቷል። ከሀገር ውስጥ ቡድኖች ጋርም የተለያዩ የአቋም መፈተሻ ጨዋታዎችሲያደርግ የቆየው ብሄራዊ ቡድኑ÷  ለዛሬው ጨዋታ የመጨረሻ ልምምዱን ትናንት በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ማከናወኑ የሚታወስ…
Read More...

በሪጋ 2023 የጎዳና ላይ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይጠበቃሉ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በላቲቪያ ሪጋ በሚካሄዱ የጎዳና ላይ ውድድሮች ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የማሸነፍ ቅድመ ግምት ተሰጥቷቸዋል፡፡ በጎዳና ውድድሩ አምስት የዓለም ሪከርድ የሰበሩ አትሌቶች የሚሳተፉ ሲሆን÷ የኦሎምፒክ እና የዓለም ሻምፒዮን አትሌቶችን ጨምሮ 347 አትሌቶች በስድስት ርቀቶች ይሳተፋሉ፡፡ ከመስከረም 20 እስከ 21 ቀን 2016…

ለዓመታት ከአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ርቆ የቆየው አርሴናል 4 ለ 0 አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 9፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ለስድስት ዓመታት ከአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ርቆ የቆየው አርሴናል በምድብ ማጣሪያ ጨዋታው ፒ ኤስ ቪ አይንዶቨንን 4 ለ 0 አሸንፏል። በተመሳሳይ በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የ2023/24 የውድድር አመት የምድብ የመጀመሪያ ጨዋታውን ያደረገው ባየር ሙኒክ ተጋጣሚውን ማንቼስተር ዩናይትድን 4 ለ 3 በሆነ ውጤት ረትቷል።…

ሪያል ማድሪድ ዩኒየን በርሊንን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 9፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ምሽቱን በተካሄደው የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የምድብ ማጣሪያ ጨዋታ ሪያል ማድሪድ ተጋጣሚውን ዩኒየን በርሊንን 1 ለ 0 አሸንፏል። ጁዲ በሊንግ ሃም በተጨማሪ ሰዓት የማድሪድን ብቸኛ ጎል ከመረብ አሳርፏል፡፡ በሌላ በኩል ኮፕንሀገን ከጋላታሳራይ ጋር ሁለት አቻ በሆነ ውጤት ተለያይተዋል፡፡ #Ethiopia…

አርሰናል ከ6 ዓመታት በኋላ የመጀመሪያ የሻምፒየንስ ሊግ ጨዋታውን ዛሬ ምሽት ያደርጋል

አዲስ አበባ ፣ መስከረም 9 ፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሰሜን ለንደኑ ክለብ ከ6 ዓመታት ቆይታ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የሻምፒየንስ ሊግ ጨዋታውን ከኔዘርላንድሱ ፒኤስ ቪ ኢንድሆቭን ጋር ዛሬ ምሽት ያደርጋል፡፡ አርሰናል ለመጨረሻ ጊዜ በመድረኩ ተሳትፎ ያደረገው በፈረንጆቹ 2017 ሲሆን÷ በዚህም በጀርመኑ ክለብ ባየርሙኒክ ከምድብ ተሸንፎ መሰናበቱ የሚታወስ ነው፡፡ በማይክል…

በአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ሁለተኛ ዙር ቅድመ ማጣሪያ ባህር ዳር ከተማ ድል ቀናው

አዲስ አበባ ፣ መስከረም 6 ፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ሁለተኛ ዙር ቅድመ ማጣሪያ ባህር ዳር ከተማ ድል ቀንቶታል። ባህር ዳር ከተማ ከቱኒዚያው ክለብ አፍሪካን ጋር ያደረገውን ጨዋታ 2 ለ 0 አሸንፏል። የድል ጎሎቹን ሀብታሙ ታደሰ ከእረፍት በፊት እና በጨዋታው መጠናቀቂያ ደቂቃዎች ላይ አስቆጥሯል። የመልሱ ጨዋታ ከቀናት በኋላ የሚካሄድ…

ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በተሳተፈችበት የ ጄ ኬ ኤስ የካራቴ ውድድር የወርቅ ሜዳሊያ አገኘች

አዲስ አበባ፣ መስከረም 6፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ)ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በተሳተፈችበት የ ጄ ኬ ኤስ (jks) የካራቴ ውድድር የወርቅ ሜዳሊያ አግኝታለች፡፡ በዱባይ እየተካሄደ ባለው የእስያ አፍሪካ ዋንጫ የjks የካራቴ ውድድር ላይ ተሳታፊ የሆኑት ሶስት ኢትዮጵያውያን ተወዳዳሪዎች ሜዳሊያ አግኝተዋል። በመድረኩ በ60 ኪሎ ግራም የተወዳደረው ናትናኤል…