Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

ብሄራዊ ቡድኑ ከሞዛምቢክ ጋር ለመጫዎት ዝግጁ ነው – አሰልጣኝ ውበቱ አባተ

አዲስ አበባ፣ ጥር 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ብሄራዊ ቡድኑ በነገው ዕለት ከሞዛምቢክ ጋር ለሚደርገው ጨዋታ ዝግጁ መሆኑን አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ተናገሩ፡፡ በነገው ዕለት የሚካሄደውን ጨዋታ አስመልክቶ የብሔራዊ ቡድኑ ዋና አሰልጣኝ ውበቱ አባተ እና አምበሉ መስኡድ መሐመድ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። አሰልጣኙ በመግለጫቸውም÷ ብሄራዊ ቡድኑ በሀገር ቤት ዝግጅት ሲያደርግ መቆየቱን እና ከጥር 4 ጀምሮ ወደ ሞሮኮ በማምራት ሁለት የዝግጅት ጨዋታዎችን ማድረጉን ገልጸዋል፡፡ ብሄራዊ ቡድኑ ከትላንት በስቲያ አልጀሪያ መድረሱን ያነሱት አሰልጣኝ…
Read More...

ዕለታዊ አጫጭር የውጭ ስፖርታዊ ዜናዎች

ቼልሲ ከ 17 ዓመት በኋላ በፕሪሚየር ሊጉ በፉልሃም 2 ለ 1 ተሸንፏል፤የትላንት ምሽቱን ውጤት ተከትሎም አሰልጣኝ ግራም ፖተርስ አጣብቂኝ ውስጥ ገብተዋል፡፡ በጨዋታው የተሰለፈው አዲሱ ፈራሚ ዣኦ ፊሊክስ ለፕሪሚየር ሊጉ የመጀመሪያ ጨዋታውን ቢያደርግም ሜዳ ውስጥ በፈጸመው ጥፋት በ58ኛው ደቂቃ በቀይ ካርድ ከሜዳ ወጥቷል፡፡ ክርስቲያኖ ሮናልዶ ከ2022 የፊፋ ምርጥ የወንድ…

 ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በቦስተን ማራቶን ይሳተፋሉ

አዲስ አበባ፣ ጥር 4፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በቦስተን ማራቶን በሁለቱም ጾታዎች እንደሚሳተፉ የውድድሩ አዘጋጆች አስታውቀዋል፡፡ በወንዶች ምድብ ሌሊሳ ዴሲሳ፣ሹራ ቂጣታ፣ አንዳምላክ በልሁ ፣ አንዱዓለም በላይ እንዲሁም ሂርጳሳ ነጋሳ በውድድሩ ይካፈላሉ፡፡ በሴቶቹ ደግሞ የዓለም የማራቶን ሻምፒዮኗ  ጎይተይቶም ገብረስላሴ  እና የኢትዮጵያን ብሔራዊ…

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለቻን ውድድር አልጄሪያ ገብቷል

አዲስ አበባ፣ ጥር 4፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቻን ውድድር አስተናጋጅ በሆነችው አልጄርያ በሰላም ገብቷል፡፡   ብሄራዊ ቡድኑ አልጀርስ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ በአልጀርያ ባህላዊ ሙዚቃ የታጀበ አቀባበል ተደርጎለታል።   ዋልያዎቹ በቻን ውድድር በምድብ አንድ ከአዘጋጇ አልጄሪያ እንዲሁም ሞዛምቢክ እና ሊቢያ ጋር…

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ወደ አልጄሪያ አቀና

አዲስ አበባ፣ ጥር 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአልጄሪያ አስተናጋጅነት በሚካሔደው ሰባተኛው የአፍሪካ እግር ኳስ ሻምፒዮና (ቻን) የሚሳተፈው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ወደ አልጀሪያ አቀና፡፡ ውድድሩ ከነገ በስቲያ ይጀመራል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለውድድሩ በአገር ውስጥ እና ከአገር ውጪ ቅድመ ዝግጅት አድርጓል። ዋልያዎቹ በቻን ውድድር በምድብ አንድ ከአዘጋጇ…

የሴቶች ፕሪሚየር ሊግና የሴቶች ከፍተኛ ሊግ 2ኛ ዙር ውድድር የሚጀመርበት ቀን ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ፣ ጥር 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሴቶች ፕሪሚየር ሊግ፣ ሴቶች ከፍተኛ ሊግ እና ከ20 ዓመት በታች ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛ ዙር ውድድር የሚጀመርበት ቀን እና የዝውውር ጊዜ ይፋ ተደርጓል።   በዚህ መሰረትም የሴቶች ፕሪሚየር ሊግ እና ሴቶች ከፍተኛ ሊግ ሁለተኛ ዙር ውድድር የካቲት 26 ቀን2015 ዓ.ም እንደሚጀመር ተገልጿል፡፡  …

አሸናፊ በቀለ የፋሲል ከነማ አሰልጣኝ ሆኑ

አዲስ አበባ፣ ጥር 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አሸናፊ በቀለ የፋሲል ከነማ አሰልጣኝ በመሆን አፄዎቹን በይፋ ተረክበዋል፡፡ ፋሲል ከነማ በዘንድሮው የሊግ ውድድር ደካማ አቋም ያሳየ ሲሆን ፥ ባደረጋቸው 13 ጨዋታዎች 17 ነጥቦችን ብቻ በመሰብሰብ 10ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡ በዚህም ክለቡ የቡድኑን አሰልጣኝ ሀይሉ ነጋሽን ቀደም ብሎ ያሰናበተ ሲሆን ፥ በምትኩ  አሰልጣኝ…