ስፓርት
40ኛው የጃንሜዳ ኢንተርናሽናል ሀገር አቋራጭ ውድድር የፊታችን እሑድ ይካሄዳል
አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 20፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) 40ኛው የጃንሜዳ ኢንተርናሽናል ሀገር አቋራጭ ውድድር የፊታችን እሑድ በሱሉልታ ከተማ እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ገለጸ።
የፌዴሬሽኑ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንት አትሌት ገዛኸኝ አበራ÷ በመጪው እሑድ በሚካሄደው 40ኛው የጃንሜዳ ኢንተርናሽናል ሀገር አቋራጭ ውድድር ከ1 ሺህ 29 በላይ አትሌቶች ይካፈላሉ ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል።
ውድድሩ ከጃንሜዳ ወደ ሱሉልታ የቦታ ለውጥ የተደረገው ጃንሜዳ ኮቪድ-19 በገባበት ወቅት የአትክልት መሸጫ ሥፍራ ሆኖ ሲያገለግል በመቆየቱ ለውድድር…
Read More...
በቻን የአፍሪካ ሀገራት ውድድር የተሻለ ውጤት ለማምጣት እንሰራለን – አሰልጣኝ ውበቱ አባተ
አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 20፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቻን የአፍሪካ ሀገራት ውድድር የተሻለ ውጤት ለማምጣት እንሰራለን ሲሉ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ገለጹ።
አሰልጣኝ ውበቱ በአልጀሪያ የሚካሄደውን 7ኛው የቻን የአፍሪካ ሀገራት ውድድር ላይ ለመሳተፍ ብሄራዊ ቡድኑ ያደረጋቸውን ዝግጅቶች አስመልክተው መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም÷ የኢትዮጵያ …
ሞሮኮ በቻን ውድድር ለመሳተፍ ቅድመ ሁኔታ አስቀመጠች
አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 19 ፣2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሞሮኮ ብሄራዊ ቡድን የሀገር ውስጥ ተጫዋቾች ብቻ በሚሳተፉበት የቻን የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ለመሳተፍ ቅድመ ሁኔታ አስቀምጧል።
ብሄራዊ ቡድኑ ከሞሮኮ አልጄሪያ የቀጥታ በረራ ካልተፈቀደለት በአልጀሪያ አስተናጋጅነት በሚካሄደው የቻን ውድድር ሊሳተፍ እንደማይችል አስታውቋል።
ቅድመ ሁኔታውን ያስቀመጠው የቻን አስተናጋጇ…
በፕሪሚየር ሊጉ ባህርዳር ከነማ እና ወላይታ ድቻ ድል ቀንቷቸዋል
አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 17፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ በተደረጉ የ7ኛ ሳምንት ተስተካካይ ጨዋታዎች ባህርዳር ከነማ እና ወላይታ ድቻ ድል ቀንቷቸዋል፡፡
ምሽት አንድ ሰዓት ላይ አርባ ምንጫ ከነማን የገጠመው ባህርዳር ከነማ ኦሴ ማውሊ ባስቆጠራቸው ግቦች 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡
ውጤቱን ተከትሎም የጣና ሞገዶቹ ከመሪው ኢትዮጵያ…
ኢንተርናሽናል ዳኛ ባምላክ ተሰማ በቻን ውድድር የቪዲዮ ረዳት ዳኛ ሆነው እንዲያጫውቱ ተመረጡ
አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 17፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢንተርናሽናል ዳኛ ባምላክ ተሰማ በአልጄሪያ አስተናጋጅነት በሚካሄደው ሰባተኛው የአፍሪካ እግር ኳስ ሻምፒዮና (ቻን) በቪዲዮ ረዳትነት እንዲያጫውቱ ተመርጠዋል።
በሀገር ውስጥ ሊግ የሚሳተፉ ተጫዋቾች ብቻ የሚሳተፉበት ውድድር ከጥር 5 እስከ 27 ቀን 2015 ዓ.ም ይከናወናል።
የአፍሪካ…
የእንግሊዝ ፕሪሚየርሊግ ከዓለም ዋንጫ መልስ ዛሬ በሚደረጉ ጨዋታዎች ይጀመራል
አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 17፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የእንግሊዝ ፕሪሚየርሊግ ከዓለም ዋንጫ መልስ ዛሬ በሚደረጉ የቦክሲንግ ደይ ጨዋታዎች ጅማሮውን ያደርጋል፡፡
ፕሪሚየር ሊጉ በኳታሩ የዓለም ዋንጫው ምክንያት ለአንድ ወር ያህል ተቋርጦ የቆየ ሲሆን ከአንድ ሳምንት እረፍት በኋላ በዛሬው እለት የሊጉ የገና ዋዜማ (ቦክሲንግ ደይ) ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡
በዚሁም መሰረት ቀን 9…
ሊዮኔል ሜሲ የፒ ኤስ ጂ ቆይታውን ለማራዘም ተስማማ
አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 15፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አርጀንቲናዊው ኮከብ ሊዮኔል አንድሬስ ሜሲ የፈረንሳዩ ፒ ኤስ ጂ ቆይታውን ለአንድ ዓመት ለማራዘም ከክለቡ ጋር ስምምነት ላይ መድረሱ ተሰማ፡፡
በሣምንቱ መጀመሪያ የስፔኑ ክለብ ባርሴሎና ፕሬዚዳንት ጆአን ላፖርታ÷ “ሜሲ 21 ዓመታትን ወዳሳለፈበት የቀድሞ ክለቡ ባርሴሎና ቢመለስ ደስ ይለኛል” ማለታቸውን ተከትሎ የሜሲ ጉዳይ…