Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

አቶ ኢሳያስ ጅራ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ሆነው በድጋሚ ተመረጡ

ዲስ አበባ፣ ነሐሴ 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ)  አቶ ኢሳያስ ጅራ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ሆነው በድጋሚ ተመረጡ። የፕሬዜዳንታዊ ምርጫው የድምፅ ቆጠራ ከደቂቃዎች በፊት የተጠናቀቀ ሲሆን፥ በውጤቱም ላለፉት አራት ዓመታት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንን በፕሬዝዳንትነት የመሩት አቶ ኢሳያስ ጅራ 94 ድምፅ በማግኘት በድጋሚ ተመርጠዋል። በእጩ ተወዳዳሪነት የቀረቡት አቶ መላኩ ፈንታ 27 ድምፅ ሲያገኙ አቶ ቶኪቻ ዓለማየሁ 17 ድምፅ ማግኘታቸውን ከፌዴሬሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
Read More...

ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአፍሪካ ሴቶች ሻምፒየንስ ሊግ የሴካፋ ዞን ማጣሪያን 3ኛ ደረጃ ይዞ አጠናቀቀ

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 21 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአፍሪካ ሴቶች ሻምፒዮንስ ሊግ የሴካፋ ዞን ማጣሪያ በሦስተኛነት አጠናቀቀ። በማጣሪያው ላይ ኢትዮጵያን የወከለው ንግድ ባንክ ዛሬ በአዛም ኮምፕሌክስ ባደረገው የደረጃ ጨዋታ የርዋንዳውን ኤ ኤስ ኪጋሊን 3 ለ 1 በማሸነፍ ሦስተኛ ደረጃ ይዞ ማጠናቀቁን ሶከር ኢትዮጵያ ዘግቧል። አረጋሽ ካልሳ፣ ሀሳቤ…

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የምርጫ ጠቅላላ ጉባዔ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 21፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጠቅላላ ጉባዔ በአዲስ አበባ የአፍሪካ የኢኮኖሚ ኮሚሽን መሰብሰቢያ አዳራሽ በመካሄድ ላይ ነው፡፡ በጉባዔው ላይ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ቀጄላ መርዳሳ፣ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር መስፍን ቸርነት፣ የዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማኅበር (ፊፋ) እና የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን…

ዋሊያዎቹ በቻን ማጣሪያ ጨዋታ 0 ለ 0 ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 20፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በቻን ማጣሪያ ከሩዋንዳ አቻው ጋር 0 ለ 0 በሆነ ውጤት ተለያይቷል፡፡ የቻን የመጨረሻ ዙር የመጀመሪያ ማጣሪያ ጨዋታ በታነዛኒያ ቤንጃሚን ምካፓ ስታዲየም ተካሂዷል፡፡ በጫወታውም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከሩዋንዳ አቻው ጋር 0 ለ 0 በሆነ ውጤት ተለያይቷል፡፡ የመልሱ ጨዋታ ከቀናት በኋላ…

“ማሜሎዲ ሳንዶውንስ”ን ለተቀላቀለው አቡበከር ናስር አቀባበል ተደረገ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 20፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ አፍሪካውን ማሜሎዲ ሳንዶውንስ የተቀላቀለውን ኢትዮጵያዊ ፕሮፌሽናል የእግር ኳስ ተጫዋች አቡበከር ናስር በደቡብ አፍሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ዶክተር ሙክታር ከድር አቀባበል አደረጉለት፡፡ በአቀባበል ሥነ-ሥርዓቱ ላይ በደቡብ አፍሪካ የተባበሩት ኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ አመራሮችም እንደተገኙም ነው የተመለከተው፡፡…

የኢትዮጵያ እና ሩዋንዳ የቻን ማጣሪያ ጨዋታ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 20፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በቻን ማጣሪያ ከሩዋንዳ አቻው ጋር ጨዋታውን እያካሄደ ነው፡፡ የቻን የመጨረሻ ዙር የመጀመሪያ ማጣሪያ ጨዋታ በታነዛኒያ ቤንጃሚን ምካፓ ስታዲየም ነው እየተካሄደ የሚገኘው፡፡ የመልሱ ጨዋታ ከቀናት በኋላ በሩዋንዳ  እንደሚካሄድ የወጣው መርሐ ግብር አመላክቷል፡፡ ጨዋታው 10 ሰዓት ላይ የጀመረ…

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በቻን ማጣሪያ ዛሬ ከሩዋንዳ ጋር ይጫወታል

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 20፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የማጣሪያ ጨዋታውን ዛሬ 10 ሰዓት ላይ ከሩዋንዳ አቻው ጋር ያደርጋል፡፡ የቻን የመጨረሻ ዙር የመጀመሪያ ማጣሪያ ጨዋታ በታነዛኒያ ቤንጃሚን ምካፓ ስታዲየም ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ እንደሚደረግ የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን መረጃ አመላክቷል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የመሀል ክፍል ተከላካዩ ያሬድ…