ስፓርት
ፈረንሳይ ጥሎ ማለፉን የተቀላቀለች የመጀመሪያዋ ሀገር ሆናለች
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 17፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በ22ኛው የኳታር የዓለም ዋንጫ ምሽት ላይ ፈረንሳይ እና ዴንማርክ የምድብ ሁለተኛ ጨዋታቸውን አድርገዋል፡፡
በዚህም ፈረንሳይ ዴንማርክን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ነጥቧን ወደ ስድስት ከፍ አድርጋለች፡፡
የፈረንሳይን የማሸነፊያ ጎሎች ክሊያን ምባፔ በ61ኛው እና 86ኛው ደቂቃ ላይ ማስቆጠር ችሏል፡፡
ዴንማርክን ከሽንፈትያላዳነችውን ብቸኛ ጎል ደግሞ አንድሪያስ ክርስቴንሰን በ68ኛውደቂቃ ላይ አስቆጥሯል፡፡
Read More...
ፖላንድ ሳዑዲ ዓረቢያን 2 ለ 0 አሸነፈች
አዲስ አበባ ፣ ሕዳር 17፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኳታር ዓለም ዋንጫ በምድብ ሶስት የሚገኙት ፖላንድ እና ሳዑዲ ዓረቢያ የሁለተኛ ዙር ጨዋታቸውን አድርገዋል፡፡
በዚህም ፖላንድ ሳዑዲ ዓረቢያን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ነጥቧን ወደ አራት ከፍ ማድረግ ችላለች፡፡
በተቃራኒው በመጀመሪያው ዙር ጨዋታ ጥሩ ተንቀሳቅሳ አርጀንቲናን ያሸነፈችው ሳዑዲ…
በዓለም ዋንጫ አውስትራሊያ ቱኒዚያን 1 ለ 0 አሸነፈች
አዲስ አበባ ፣ ሕዳር 17፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኳታር የዓለም ዋንጫ በምድብ አራት የሚገኙት ቱኒዝያ እና አውስትራሊያ የሁለተኛ ዙር ጨዋታቸውን አድርገዋል፡፡
በዚህም አውስትራሊያ አፍሪካዊቷን ቱኒዚያን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፋ ከምድቡ የማለፍ ተስፋዋን አለምልማለች፡፡
የአውስትራሊያን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ሚቸል…
በዓለም ዋንጫው አርጀንቲና ከሜክሲኮ ወሳኙን ጨዋታ ያደርጋሉ
አዲስ አበባ ፣ ሕዳር 17 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኳታሩ የዓለም ዋንጫ ዛሬ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ።
በዛሬው ውሎ የምድብ ሶስት እና አራት ቡድኖች ሁለተኛ የምድብ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
በምድብ ሶስት አርጀንቲና ከሜክሲኮ እንዲሁም በምድብ አራት ፈረንሳይ ከዴንማርክ የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ሆኗል።
በተለይም በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ ሳይጠበቅ በሳዑዲ አረቢያ…
በምድብ 1 ኔዘርላንድስ እና ኢኳዶር ነጥብ ሲጋሩ ኳታር የመጀመሪያዋ ተሰናባች ሆናለች
አዲስ አበባ ፣ ሕዳር 16 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በዓለም ዋንጫው ምድብ 1 ኔዘርላንድስ እና ኢኳዶር ነጥብ ተጋርተው ወጥተዋል።
ሁለቱ ቡድኖች ምሽት 1 ሰአት ላይ ባደረጉት ጨዋታ የዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ፈጣን ጎል ተመዝግባለች።
ጨዋታው አንድ አቻ ሲጠናቀቅ ኮዲ ጋክፖ ለኔዘርላንድስ ኤነር ቫሌንሺያ ደግሞ ለኢኳዶር ጎሎችን አስቆጥረዋል።…
ኔይማር በጉዳት ምክንያት ከሁለት የምድብ ጭዋታዎች ውጭ መሆኑ ተረጋገጠ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 16፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ብራዚላዊው የፊት መስመር ተጫዋች ኔይማር ጁኒየር በጉዳት ምክንያት በሁለት የምድብ ጭዋታዎች እንደማይሰለፍ ተገለፀ፡፡
ኔይማር ትናንት ምሽት ብራዚል ከሰርቢያ ጋር ባደረገችው ጨዋታ ላይ ባጋጠመው የቁርጭምጭሚት ጉዳት ምክንያት ነው ከሁለት የምድብ ጨዋታዎች ውጭ የሆነው፡፡
የብራዚል ብሄራዊ ቡድን ዶክተሮች ከሰርቢው ጨዋታ…
በዓለም ዋንጫ አፍሪካዊቷ ሴኔጋል ኳታርን 3ለ1 አሸነፈች
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 16፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በዓለም ዋንጫ የምድብ 2 የሁለተኛ ዙር ጨዋታ አፍሪካዊቷ ሴኔጋል አዘጋጇን ሀገር ኳታር 3 ለ 1 አሸንፋለች፡፡
በኳታር አልቱማም ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ቡሊያን ዲያ፣ ፋሙራ ዴዴሁ እና ባባ ዲየንግ የሴነጋልን ጎሎች ሲያስቆጥሩ ሞሃመድ ሞንታሪ የኳታርን ብቸኛ ጎል አስቆጥሯል፡፡
የቴራንጋ አንበሶቹ በኔዘርላንድስ…