ስፓርት
በዓለም ዋንጫው የምድብ ሁለተኛ ጨዋታዎች ዛሬ ይጀምራሉ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 16፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ዛሬ አፍሪካዊቷ ሴኔጋል የምትሳተፍበትን ጨምሮ አራት የምድብ ሁለተኛ ጨዋታዎች ይከናወናሉ፡፡
በዚህም በምድብ ሁለት የተደለደሉት ዌልስ ከኢራን ቀትር 7 ሰዓት ላይ የሚጫወቱ ሲሆን ÷ በተመሳሳይ በዚሁ ምድብ የሚገኙት እንግሊዝ ከአሜሪካ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያካሂዳሉ፡፡
በሌላ የጨዋታ መርሐ ግብር በምድብ አንድ የሚገኙት የዘንድሮው የዓለም ዋንጫ አዘጋጇ ሀገር ኳታር ከአፍሪካዊቷ ሴኔጋል ቀን 10 ሰዓት ላይ ይጫወታሉ፡፡
በዚሁ ምድብ የሚገኙት ኔዘርላንድስ ከኢኳዶር ምሽት 1 ሰዓት ላይ…
Read More...
በዓለም ዋንጫ ጨዋታ ፖርቹጋል ጋናን 3 ለ 2 በሆነ ውጤት አሸነፈች
አዲስ አበባ ፣ ሕዳር 15 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በ22ኛው የኳታር ዓለም ዋንጫ ጨዋታ የአምስተኛ ቀን ውሎ በምድብ ስምንት በተደረገ ጨዋታ ፖርቹጋል ጋናን 3 ለ 2 በሆነ ውጤት አሸንፋለች፡፡
የፖርቹጋልን የመጀመሪያ ግብ ክሪስቲያኖ ሮናልዶ በፍጹም ቅጣት ምት በ65 ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል፡፡
ጃኦ ፍሊክስ እና ራፋይል ሌዮ ደግሞ 78 ኛው እና 80ኛው ደቂቃ ላይ የፖርቹጋልን…
በዓለም ዋንጫ ጨዋታ ስዊዘርላንድ ካሜሮንን 1 ለ 0 አሸነፈች
አዲስ አበባ፣ ህዳር 15፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ሌላኛዋ የአፍሪካ ተወካይ ካሜሮን በኳታር የዓለም ዋንጫ ጨዋታ በሀገሯ ልጅ በተቆጠረባት ግብ በስዊዘርላንድ 1 ለ 0 በሆነ ውጤት ተሸንፋለች፡፡
በጨዋታው ብሪል ኤምቦሎ ከሽኮርዳን ሻኪሪ የተሻገረለትን ኳስ ወደ ግብ ቀይሮ ስዊዘርላንድ የመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋን እንድታሸንፍ አድርጓል፡፡
በትውልድ ካሜሮናዊ በዜግነት…
በዛሬው የዓለም ዋንጫ ሁለት የአፍሪካ ሀገራት የሚሳተፉበትን ጨምሮ አራት ጨዋታዎች ይካሔዳሉ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 15፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አምስተኛ ቀኑን በያዘው የዓለም ዋንጫ ውሎ ካሜሮን እና ጋና የሚሳተፉበትን ጨምሮ አራት ጨዋታዎች ይከናወናሉ፡፡
በዚሁ መሰረት በምድብ ሰባት የተደለደሉት አፍሪካዊቷ ካሜሮን ከስዊዘርላንድ ቀን ሰባት ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያከናውናሉ፡፡
በዚሁ ምድብ የተደለደሉት ብራዚል እና ሰርቢያ ምሽት አራት ሰዓት ላይ…
ስፔን ኮስታሪካን ከግማሽ ደርዘን ጎል በላይ በማስቆጠር አሸነፈች
አዲስ አበባ ፣ ሕዳር 14 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በዓለም ዋንጫው አራተኛ ቀን ውሎ ስፔን ከግማሽ ደርዘን ጎል በላይ በማስቆጠር አሸንፋለች።
በምድብ 5 የተደለደለችው ስፔን የደቡብ አሜሪካዋን ኮስታሪካን 7 ለ 0 በሆነ ሰፊ የጎል ልዩነት ማሸነፍ ችላለች።
ዳኒ ኦልሞ፣ ማርኮ አሴንሲዮ፣ ጋቪ፣ ካርሎስ ሶለር እና አልቫሮ ሞራታ አንድ አንድ ጎሎችን ሲያስቆጥሩ ፌራን ቶሬስ…
በዓለም ዋንጫ ጨዋታ ጃፓን ጀርመንን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸነፈች
አዲስ አበባ ፣ ሕዳር 14 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በ22ኛው ዓለም ዋንጫ የአራተኛ ቀን ውሎ በምድብ አምስት በተደረገ ጨዋታ ጃፓን ጀርመንን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፋለች፡፡
የማንችስተር ሲቲው የአማካይ ክፍል ተጫዋች ኢልካይ ጉንዶጋን በ33ኛው ደቂቃ በፍጹም ቅጣት ምት ያስቆጠረው ግብ የጀርመን ብሔራዊ ቡድንን መሪ ማድረግ ችሎ ነበር።
ይሁንና ተቀይሮ የገባው የጀርመኑ…
በአራተኛ ቀን የ22ኛው የዓለም ዋንጫ ውሎ አራት ጨዋታዎች ይከናወናሉ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 14፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በዛሬው የዓለም ዋንጫ የጨዋታ መርሐ ግብር አራት ጨዋታዎች ይከናወናሉ።
በዚሁ መሰረት 7 ሰዓት ላይ በምድብ ሥድስት የተደለደሉት ሞሮኮ እና ክሮሺያ ይጫወታሉ።
በተመሳሳይ በዚሁ ምድብ የሚገኙት ቤልጂየም ከካናዳ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያከናውናሉ።
በሌላ የጨዋታ መርሐ ግብር በምድብ አምስት የተደለደሉት ጀርመን…