Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

ሊግ ኩባንያው በ8ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ላይ በቀረቡ የሥነ ምግባር ጉዳዮችላይ ውሳኔ አሳለፈ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 12፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በ8ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ላይ በቀረቡ የሥነ ምግባር ጉዳዮች ላይ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡ በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 8ኛ ሳምንት በተደረጉ ስምንት ጨዋታዎች አምስት ጨዋታዎች በመሸናነፍ እና ሶስት ጨዋታዎች በአቻ ውጤት ሲጠናቀቁ 23 ጎሎች በተቆጥረዋል። በሳምንቱ 35 ተጫዋቾችና የቡድን አመራሮች የማስጠንቀቂ ቢጫ ካርድ ሲሰጣቸው አንድ ተጫዋች በቀይ ካርድ ከሜዳ ወጥቷል። የሊግ ኩባንያው ውድድር አመራርና ሥነ-ስርዓት ኮሚቴ ባደረገው…
Read More...

በኳታሩ የዓለም ዋንጫ ዛሬ ሦስት ተጠባቂ ጨዋታዎች ይከናወናሉ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 12፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በ2022 የኳታሩ የዓለም ዋንጫ የሁለተኛ ቀን ውሎ ዛሬ ሦስት ተጠባቂ ጨዋታዎች ይከናወናሉ፡፡ በምድብ ሁለት የሚገኙት እንግሊዝ እና ኢራን ከቀትር በኋላ 10 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። በጉዳት ሳዲዮ ማኔን ያጣችው ሴኔጋል ከኔዘርላንድስ ጋር ምሽት 1 ሰዓት ላይ የመጀመሪያ ጨዋታዋን ታደርጋለች።…

በዓለም ዋንጫ የመክፈቻ ዕለት አስተናጋጇ ኳታር በኢኳዶር 2 ለ 0 ተሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 11፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) 22ኛው የዓለም ዋንጫ በደማቅ ሥነ ስርዓት ዛሬ ተጀምሯል። አስተናጋጇ ኳታር ከደቡብ አሜሪካዋ ኢኳዶር ጋር የመክፈቻ ጨዋታዋን አድርጋለች። በጨዋታውም ኳታር በኢኳዶር 2 ለ 0 ተሸንፋለች ኳታር ከዛሬ ጀምሮ እስከ ፈረንጆቹ ታህሳስ 18 ቀን 2022 ድረስ ለምታስተናግደው 22ኛው የዓለም ዋንጫ ስምንት ስታዲየሞች…

የዓለም ዋንጫ የመክፈቻ ሥነ ስርዓት ተካሔደ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 11፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) 22ኛው የዓለም ዋንጫ የመክፈቻ ሥነ ስርዓት በድምቀት ተካሂዷል፡፡ የመክፈቻ ሥነ ስርዓቱ የተካሔደው በዛሬው ዕለት የመጀመሪያ ጨዋታ እያስተናገደ በሚገኘው እና 60 ሺህ ተመልካቾችን በሚያስተናግደው አል ባይት እስታዲየም ነው፡፡ በመክፈቻ ሥነ ስርዓቱ ላይ የውድድሩ ሳውንድ ትራክ ተብሎ በፊፋ ዕውቅና የተሰጠው “ሃያ ሃያ”…

በማራቶን ሪሌይ ውድድር የኦሮሚያ ፖሊስ አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 11፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሠመራ ከተማ በተካሔደው 18ኛው የኢትዮጵያ ማራቶን ሪሌይ ውድድር ኦሮሚያ ፖሊስ አሸንፏል፡፡ በክለቦች መካከል በተካሔደው የማራቶን ሪሌይ ውድድር÷ የኦሮሚያ ፖሊስ አንደኛ በመሆን የወርቅ ሜዳሊያና የገንዘብ ተሸላሚ ሆኗል፡፡ በዚሁ የውድድር መርሐ ግብር ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቀቀው የፌደራል ማረሚያ ቤቶች ገንዘብና…

ካሪም ቤንዜማ ከዓለም ዋንጫ ውጭ ሆነ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 11፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ፈረንሳዊው አጥቂ ካሪም ቤንዜማ ባጋጠመው ጉዳት ምክንያት ከዓለም ዋንጫ ጨዋታ ውጪ መሆኑን ብሔራዊ ቡድኑ አስታውቋል፡፡ ካሪም ቤንዜማ ከውድድሩ ውጭ የሆነው በትናንትናው ዕለት በልምምድ ላይ ሳለ ባጋጠመው የጡንቻ ጉዳት መሆኑን የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን በማህበራዊ ትስስር ገጹ ይፋ አድርጓል፡፡ የ2022 የባሎንዶር አሸናፊው…

የዘንድሮውን ታላቁ ሩጫ በወንዶች አትሌት አቤ ጋሻው ለሦስተኛ ጊዜ አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 11፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የዘንድሮውን ታላቁ ሩጫ በወንዶች ከአማራ ማረሚያ ቤት አትሌት አቤ ጋሻው አሸንፏል፡፡ አትሌት አቤ ጋሻው የዘንድሮውን ሲያሸንፍ ለሦስተኛ ጊዜ መሆኑን ተናግሯል፡፡ አትሌት ኃይለማርያም አማረ ከፌደራል ማረሚያ ሁለተኛ እና አትሌት ገመቹ ዲዳ ከኢትዮ ኤሌክትሪክ ሦስተኛ ደረጃን በመያዝ የዘንድሮውን ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ…