ስፓርት
ግብፅ በኢትዮጵያ ከገጠማት መራር ሽንፈት በኋላ አሰልጣኟን አሰናበተች
አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 9 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የግብፅ እግር ኳስ ማህበር የብሄራዊ ቡድኑን አሰልጣኝ ኢሀብ ጋላልን ከአሰልጣኝነት አሰናበተ።
ግብጽ የዛሬ ሳምንት ለአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ሁለተኛ ጨዋታዋን በኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከጨዋታ ብልጫ ጋር 2 ለ 0 መሸነፏ ይታወሳል።
ከዚህ ባለፈም በወዳጅነት ጨዋታ ከትናንት በስትያ በደቡብ ኮሪያ የ4 ለ 1 ሽንፈት አስተናግዳለች።
ከደቂቃዎች በፊት ይፋ በሆነው መረጃ መሰረት ደግሞ የሀገሪቱ የእግር ኳስ ማኅበር የብሔራዊ ቡድኑን አሠልጣኝ ከመንበሩ ማንሳቱን ይጠቁማል።
የ54 ዓመቱ አሠልጣኝ…
Read More...
በፕሪሚየር ሊጉ ጅማ አባ ጅፋር እና ፋሲል ከነማ ድል ቀንቷቸዋል
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በ26ኛ ሳምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጅማ አባ ጅፋር ሃድያ ሆሳዕናን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡
ረፋድ ላይ በተደረገው ጨዋታ አንጋፋው ዳዊት እስጢፋኖስ ከረጅም ጊዜ በኋላ ባስቆጠራት ጎል ጅማ አባ ጅፋር ሙሉ ሶስት ነጥብ ማግኘት ችሏል፡፡
በ23 ነጥብ ወራጅ ቀጠና ውስጥ የሚገኘው ጅማ አባ ጅፋር የዛሬው ድል…
በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየርሊግ ኢትዮጵያ ቡና አዳማ ከተማን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ሰኔ 8፣2014 (ኤፍ ቢሲ) በ26ኛ ሳምንት የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና አዳማ ከተማን 2 ለ 1 አሸንፏል፡፡
በባህርዳር ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ አዳማ ከተማ እስከ እረፍት በአሜ መሀመድ ብቸናኛ ጎል ሲመራ ቢቆይም ከዕረፍት መልስ አቡበከር ናስር ያስቆጠራቸው ጎሎች ቡናማዎችን አሸናፊ አድርገዋል፡፡
ኢትዮጵያ ቡና ማሸነፉን ተከትሎ…
ከዕረፍት በተመለሰው ፕሪሚየር ሊግ አርባ ምንጭ ከተማ ድል ቀንቶታል
አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 7 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የቤት ኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከዕረፍት መልስ ዛሬ ተካሂዷል።
ረፋድ ላይ ሲዳማ ቡናን ከአርባ ምንጭ ከተማ ባገናኘው ጨዋታ አርባ ምንጭ አሸናፊ ሆኗል።
ጨዋታው 2 ለ 1 ሲጠናቀቅ ኤሪክ ካፓይቶ ሁለቱን የማሸነፊያ ጎሎች ለአርባ ምንጭ ከተማ አስቆጥሯል።
የሲዳማ ቡና ማስተዛዘኛ ጎል ደግሞ…
በግብፅ የተመዘገበው ድል የብሄራዊ ቡድኑን ጥንካሬ የሚያሳይ ነው-አሰልጣኝ ውበቱ አባተ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 6፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በግብፅ የተመዘገበው ድል የብሄራዊ ቡድኑን ጥንካሬ የሚያሳይ ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ገለጹ፡፡
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ቆይታውን በተመለከተ የቡድኑ አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡
አሰልጣኙ በመግለጫቸው ዋሊያዎቹ የግብፅን ብሄራዊ ቡድን ከማሸነፍ…
ኢትዮጵያ በ22ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና 5ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች
አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 5 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ በ22ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና 5ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች።
በውድድሩ ኢትዮጵያ በ4 ወርቅ፣ 6 ብር እና 4 ነሃስ በአጠቃላይ በ14 ሜዳልያ 5ኛ ደረጃ ይዛ ማጠናቀቋን የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን መረጃ ያመላክታል።
በውድድሩ የመጨረሻ ቀን በሴቶች 3 ሺህ መሰናክል እና በ5 ሺህ ወንዶች ውድድር ሁለት የወርቅ…
በ22ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ ተጨማሪ የወርቅ ሜዳልያ አገኘች
አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 5 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በ22ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ ተጨማሪ የወርቅ ሜዳልያ አግኝታለች።
ዛሬ በተካሄዱ ውድድሮች በ3 ሺህ ሜትር መሰናክል ሴቶች ኢትዮጵያ የወርቅና የብር ሜዳልያ አግኝታለች።
በውድድሩ አትሌት ወርቁውሃ ጌታቸው እና ዘርፌ ወንድማገኝ አንደኛ እና ሁለተኛ በመውጣት የወርቅና የብር ሜዳልያዎችን አስገኝተዋል።…