Fana: At a Speed of Life!

በአሜሪካ ከፍተኛ ሙቀት ያስነሳው የሰደድ እሳት በፍጥነት እየተስፋፋ መሆኑ ተነገረ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 19፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአሜሪካ በተከሰተው ከፍተኛ የአየር ሙቀት ምክንያት የሰደድ እሳት በፍጥነት እየተስፋፋ መምጣቱና በጤናም ላይ ከፍተኛ ችግር እየፈጠረ መሆኑ ተነገረ፤

በአሜሪካ በካሊፎርኒያ ዮሴሚት ብሔራዊ ፓርክ አቅራቢያ ከፍተኛ የሆነ የሰደድ እሳት በፍጥነት መስፋፋቱን ተከትሎ በአካባቢው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ታውጇል።

ክስተቱ ለአካባቢው ነዋሪዎች የጤና ስጋት ማስከተሉም ተገልጿል፡፡

በሺዎች በሚቆጠር ሄክታር መሬት ላይ እየተስፋፋ የሚገኘው የሰደድ እሳት ከ6 ሺህ በላይ ነዋሪዎች አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ ማስገደዱ ተነግሯል።

የካሊፎርኒያ በሰደድ እሳት መንደድ አብዛኛው የአገሪቱ ክፍል በሙቀት ማዕበል እንዲናወጥ አድርጎታልም ተብሏል፡፡

ችግሩን ተከትሎ በተቀሩት የሀገሪቱ ግዛቶች የማስጠንቀቂያ መልዕክቶች በስፋት እየተላለፉ እንደሆነም የሲጂቲኤን ዘገባ አመላክቷል፡፡

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.