Fana: At a Speed of Life!

ኪሊያን ምባፔ ወደ ማድሪድ ተመለሰ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ26 ዓመቱ ተጫዋች ኪሊያን ምባፔ ባጋጠመው ጉዳት ምክንያት ወደ ሪያል ማድሪድ ተመልሷል፡፡

ትናንት ምሽት ፈረንሳይ በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ዩክሬንን 4 ለ 0 ባሸነፈችበት ጨዋታ ሁለት ግቦችን ቢያስቆጥርም ጉዳት አጋጥሞታል፡፡

በዚህም ተጫዋቹ የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን ስብስብን በመልቀቅ ወደ ክለቡ ሪያል ማድሪድ ለመመለስ ተገድዷል፡፡

ኪሊያን ምባፔ በቀኝ ቁርጭምጭሚቱ ላይ እብጠት እንዳጋጠመው የተገለፀ ሲሆን÷ ተጨማሪ የሕክምና ምርመራ በማድሪድ እንደሚደረግለት ነው የተጠቆመው፡፡

ፈረንሳዊው የፊት መስመር ተጫዋች ባጋጠመው ጉዳት ምክንያት በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ የመጨረሻ ጨዋታ ሀገሩ ፈረንሳይ ከአዘርባጃን የምታደርገው ጨዋታ የሚያልፈው ይሆናል፡፡

ፈረንሳይ ትናንት ምሽት ዩክሬንን በማሸነፍ ለ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ውድድር ማለፏ ይታወቃል፡፡

በጨዋታው ሁለት ግብ ያስቆጠረው ኪሊያን ምባፔ በእግር ኳስ ሕይወቱ ያስቆጠራቸውን የግብ ብዛት ወደ 400 ከፍ ማድረግ ችሏል፡፡

በወንድማገኝ ፀጋዬ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.