የአማራ ክልል ምክር ቤት 12ኛ መደበኛ ጉባኤ መካሄድ ጀመረ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአማራ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 12ኛ መደበኛ ጉባኤውን በባህርዳር ከተማ ማካሄድ ጀምሯል።
በጉባኤው የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ይደረግበታል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በተጨማሪም ልዩ ልዩ አዋጆች እና የ2019 የክልሉ በጀት ለምክር ቤቱ ቀርቦ እንደሚጸድቅ ይጠበቃል ሲል አሚኮ ዘግቧል።