Fana: At a Speed of Life!

የሲዳማ ክልል ወጣቶችና ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች #በቃ በማለት ድምፃቸውን አሰሙ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 15፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሲዳማ ክልል ብልፅግና ፅ/ቤት መርሃ ግብር ላይ የሐዋሳ ከተማ ወጣቶችና ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች #በቃ የሚለውን ንቅናቄ አንግበው በመሰለፍ የውጭ ሀገራት ጫና ሊቆም ይገባል ብለዋል፡፡

የጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ግንባር መዝመትም ትልቅ መነሳሳት እንደፈጠረባቸው ተናግረው ÷ አቅማቸው በፈቀደው ደረጃ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጎን እንደሚቆሙ ያላቸውን አቋም አሳይተዋል፡፡

ወጣት ቤተልሔም አያኖ እድሜዋ ቢፈቅድ የመዝመት ፍላጎት እንዳላት ገልጻ ÷ አባቷም በጦር ሜዳ ለእናት ሀገሩ እየተዋጋ እንደሚገኝና ከአባቷ ጋር ድል የመቀናጀት ትልቅ ፍላጎት እንዳላት ተናግራለች፡፡

በእንባና በወኔም ሆና “ ምዕራባዊያን ከምወዳት ሀገሬ ላይ እጃችሁን አንሱ” ብላለች፡፡

የጠቅላይ ሚኒስተሩ መዝመት ከፍተኛ መነሳሳት እንደፈጠረባቸው የገለፁት ወጣት ኃይለ ኢየሱስ ታምራትና ወጣት ሳራ አብርሃም ÷ እነሱም በሚፈለግበት ጉዳይ ሁሉ ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

የጠቅላይ ሚኒስትሩ በግንባር መገኘት እንዳኮራቸው በመግለፅ ሁሌም ከጎናቸው ነን ብለዋል፡፡

ወጣቶቹ ÷ ኢትዮጵያ ላይ ጫና ለማሳደር የሚጥሩ የውጭ ኃይሎችም እጃቸውን እንዲያነሱ ለማሳወቅ በማሰብ በጠዋት ተሰባስበው መውጣታቸውን ተናግረዋል፡፡

በዝግጅቱ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የሲዳማ ክልል ብልፅግና ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አብርሃም ማርሻሎ ÷ ኢትዮጵያዊያን እያለን ሀገር አትፈርስም ፤ በሲዳማ የምትገኙ ወጣቶችም “በቃ”ን በመቀላቀል የኢትዮጵያን እውነት ማሳየት ይገባል ብለዋል፡፡

ሠልፈኞቹ ÷ እኔ እያለው ኢትዮጵያ አትደፈርም ! በቃ ሊባሉ ይገባል በሚል እየተካሄደ የሚገኘው ንቅናቄም ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል፡፡

በብርሃኑ በጋሻው
አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.